ወጣት ሜሮን ያለ አንዳች ጥፋት በተደጋጋሚ በበሬ ወለድ ክሶች ለእስር እንደተዳረገች እና በእስር በነበረችበት ዘጠኝ ወራቶች ውስጥ የህወሃት መርማሪዎች በሷና በሌሎች የህሊና ታሳሪዎች ላይ የፈፀሙትን አሰቃዊ ግፎች በቃለ መጠይቋ አስታውሳለች።
ወጣት ሜሮን በአሁኑ ሰዓት ኤርትራ የሚገኙትን የነጻነት ኃይሎች ተቀላቅላ ትገኛለች። አርበኛ ታጋይ ሜሮን በአገሬ ላይ የተጫነውን አምባገነናዊ ስርዓት ለማስወገድ በሚደረገው ትግል ነፍሴን ልሰጥ በረሃ ገብቻለሁ ስትል ተደምጣለች።
በመጨረሻም ወጣቷ ባስተላለፈችው መልእክት “ሁላችንም እራሳችንን ነፃ ማውጣት አለብን። በብዛት ሲታይ የተወሰነ ሰው መስእዋት ከፍሎ ሌላው ተደስቶ መኖር ነው የሚፈልገው ፤ ነገር ግን ሁላችንም መታገል ብንችል ከዚህ አንባገነን ስርአት ነፃ መውጣት እንደምንችል እንዲረዱልኝ እፈልጋለሁ።” ብላለች።
የአርበኞች ግንቦት 7 ድምጽ ሬድዮ
No comments:
Post a Comment