
1. ወያኔ እና ግብረአበሮቹ ከኢትዮጵያ እያስመጡ የሚሸጡዋቸው ሸቀጦችን፣ እንጀራ፣ቡና፣ መጠጥ፣ ጤፍ ድቄት፣ የመሳሰሉትን አንገዛም፣
2. ወደ ኢትዮጵያ ለመጓዝ የታሰቡ እቅዶቻችንን እንሰርዛለን ወይም ለሌላ ጊዜ እናስተላልፋለን፣
3. ኢትዮጵያ ውስጥ ኢንቨስትመንት ለማድረግ የሚያስቡ ኢትዮጵያዊያን ፤ የውጭ ዜጎችና ድርጅቶች እቅዳቸውን እንዲያዘገዩ እናግባባለን፣
4. ህወሃት ለህዝባችን ፍቃድ እስኪንበረከክ ድረስ ለወያኔ ባለሥልጣናትና ለሥርዓታቸው ከፍተኛ የገቢ ምንጭ በሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ መጠቀም እናቆማለን። አስቸኳይ ጉዳይ ገጥሞን ወደ አገር ቤት ለመጓዝ ከተገደድን ሌላ አየር መንገዶችን እንጠቀማለን፣
5. በወያኔና የጥቅም ሸሪኮቹ የሚሰጡ ማናቸውም ዓይነት አገልግሎቶች ከመጠቀም እንቆጠባለን፣
6. የወያኔ አባላትና ደጋፊዎች ከአገዛዙ ጋር ያላቸውን ቁርኝት ካላቋረጡ ከየትኛውም ማህበራዊ ግንኙነት እናገላቸዋለን፣
7. የህወሃት ባለሥልጣናት ከአገር ዘርፈው ወደ ውጪ የሚያሸሹት ገንዘብና ንብረት እየተከታተልን እንመዘግባለን፤
8. ህዝባችንን የሚያስጨፈጭፉ ፤ የሚያሳስሩና የሚያስገርፉ ወደ ውጭ ሲመጡ እግር እግራቸውን እየተከታተልን እናጋልጣቸዋለን፤ እናሸማቅቃቸዋለን!
No comments:
Post a Comment