
አብዛኞቹ የአጋዚ ጦር አባላት በአብዛኛው በኦሮምያ ሻሸመኔ አካባቢ እንደሚገኙ ተናግረዋል። የአጋዚ ጦር አባላት ቁጥር መመናመኑን ተከትሎ ከአጋዚ ጦር ውጭ ያሉ ወታደሮች እንዲመደቡ መደረጉንም ገልዋጸል። የአጋዚ ጦር አባላት ሁኔታዎች ቢመቻችላቸው ሁሉም ከሰራዊቱ ለመልቀቅ ፈቀዳኛ ናቸው የሚሉት አባላቱ፣ በአሁኑ ጊዜ አጋጣሚውን እየፈለገ የሚወጣውን ወታደር ለመተካት አዲስ ምልምል ወታደሮችን ማግኘት አልተቻለም ይላሉ።
በሶማሊያ በአጋዚ ጦር አባላት ላይ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱንም ወታደሮቹ ተናግረዋል። ሶማሊያ ገብተው ከፍተኛ መስዋትነት ቢከፍሉም፣ በመልሱ ምንም ጥቅም አለማግኘታቸውን ተናግረዋል። ከዚህም በላይ ከሻለቃ በላይ ያሉት አዛዦች ከአንድ ብሄር የተውጣጡ በመሆናቸውና ትእዛዝ የሚሰጡትም እነሱ በመሆናቸው፣ ተራው ወታደር ሊቃወም ቢሞክር በቀጥታ እርምጃ ይወሰድበታል ሲሉ ኢሳት በቡድን ያነጋገራቸው አባላቱ ተናግረዋል።
No comments:
Post a Comment