Wednesday, August 12, 2015

ጥቂት ስለ አቶ መለስ…የክፋት ጭንቅላት መስራት ካቆመ 3 አመቱ = በክፋት የተጨመቁ መሃይማን ግዞት ቀጥሏል - See more at: http://www.zehabesha.com/amharic/archives/45825#sthash.R5UsY9rB.dpuf

መለስ ዜናዊ ከጅምሩ በክፋት የሰለጠነ መሆኑ እሙን ነው:;ድርጊቶቹ ሁሉ ይመሰክራሉ::አስተዳደጉ እንኳን ብናየው ከቀሪው ኢትዮጵያዊ ላይ ከፍተኛ የሆነ የጥላቻ ተረት ተረት እየተነገረው ያደገ ሲሆን በእድገት ዘመኑ እናትና አባቱ ብሎም የቅርብ ዘመዶቹ ሲናገሩ የሚሰማው የጣሊያንን ደግነት እና የኢትዮጵያውያንን ሃጢያተኝነት በተለይ የንጉሰነገስቶችን እና የአማራን ጥላቻ ሲሰበክ ያደገ የሰላቶ አገልጋዮች የባንድ ልጅ መሆኑ ይታወቃል::እንደዚህ አይነት ግለሰብ ለኢትዮጵያ ደግ ያስባል ለኢትዮጵያውያን መልካምነትን ይመኛል ማለት ከዘበትም በላይ በድርጊት የታየ ነው::ታሪክን የኋሊዮሽ ካየን በባንዳ ቤተሰብ ውስጥ ያደጉ ሰዎች እስከዛሬ ስለሃገር እና ስለሕዝብ የማያስቡ የጀርባ ቅማሎች ሆነው እያየናቸው ነው::
11231209_1623159974621065_3459709504333964141_n

በባንዳ ቤተሰብ ውስጥ የነጮችን የበላይነት ሲሰበክ ያደገው መለስ ዜናዊ በኢትዮጵያውያን ላይ ያለው ጥላቻ ካደገ በኋላ ወደ መሃል አገር በሚያየው የኢትዮጵያውያን ደግነት እና ጨዋነት እንዲሁም ፍቅር ከመማረክ ይልቅ በቅናት እና ባደገበት ጥላቻ ተመርኩዞ የበታችነት ስሜቱ ስላጠላበት ትምህርቱን ጥሎ መሰደዱም ሌላኛው ባዶነቱን ያሳያል::በረሃም ገብቶ ለኢትዮጵያውያን ያልተኛው መለስ ዜናዊ በአላማ የማይለዩትን የተማሪ ቤት አጋሮቹን የሆኑትን የኢሕአፓ አባላት በመፍጀት እና በማስፈጀት ለሞት ለእስር እና ለስደት ዳርጓቸዋል::በበረሃ ቆይታው ከፍተኛ ወንጀሎችን በመስራት ከተባባሪዎቹ ከነስብሃት ነጋ ጋር በመሆን ወደ ከፍተኛ እርከን የደረሰው ይህ ሰው እጁ ከበለሃ ጀምሮ በደም የተነከረ ለአገር ይጠቅማሉ የተባሉ በርካታ ታጋዮችን ያጠፋ ሲሆን አብዛኛዎቹ ታጋዮች ሊጠፉ የቻሉት ኢትዮጵያዊ ከሚል የሃሳብ መደርደሪያ በመነሳታችው መሆኑ አንዱ ምክንያት ሲሆን በአስተሳሰብ ልዩነት አሊያም በልጠው የተገኙትን በማስገደል እና እንዲሰደዱ በማድረግ ከፍተኛ ሚና ተጫውቷል::
መለስ ዜናዊ ሱዳን ላይ ተቀምጦ አንድ ጥይት ሳይተኩስ በልጅነቱ ከጓደኛው ጋር ሲደባደብ የተፈነከተውን ጠባሳ ይዞ ጥይት መቶኝ ነበር በማለት ከፍተኛ በሃሰት የተሞላ ጀግንነት እና ጀብደኝነት ሲያወራ የነበር የሃሰት ሰው ነበር::ማንበብ የሚወደው የማኪያቬሊዝም ፍልስፍና ተከታይ የሆነው መለስ ዜናዊ ከበረሃ በኋላ በሃገር ድረጃ ስልጣን ከያዘ ጀምሮ ከፍተኛ ወንጀሎችን ብመላው ኢትዮጵያውያን ላይ ፈጽሟል::ትዘርዝሮ የማያልቅ የፖለቲካ የኢኮኖሚ እና የማህበራዊ ወንጀሎችን የፈጸመው መለስ ዜናዊ ኢትዮጵያውያን ካለቤተሰብ በትኗል አስገድሏል አሰድዷል አስሯል በአንድ አገር ውስጥ መሪ ነኝ ከሚል አንድ ባለስልጣን የማይጠበቅ ሁኔታ በዜጎች ላይ ከፍተኛ ታሪክ ይቅር የማይለው ከሱ በፊት የነበሩ መንግስታት ያልፈጸሙትን በገሃድ እና በሕቡእ ከባባድ ወንጀሎች ፈጽሟል::የመለስ ዜናዊ ወንጀሎች ተዘርዝረው አያልቁም::በአለም አቀፍ ደረጃ ቱጃር ከሚባሉት የአገር መሪዎች ግንባር ቀደም የነበረው መለስ ዜናዊ የሃገራችንን አንጡረ ሃብት ርሕራሄ በሌለው ሁኔታ ከነሚስቱ እና አሾክሻኪዎቹ ጋር በመሆን ዘርፏል::
የመለስ ዜናዊን ወንጀል ተንቶ ለመጻፍ እጅግ ብዙ ጊዜ ይወስዳል::በስልጣን ዘመኑ አንድ ቀን ሃገሬ ሳይል “ይህቺ ሃገር…” ምናምን እንዳለ ሕዝብን እየተሳደብ ሲያፈናቅል እና ሲያሸማቅቅ የሞተው ይህ ከይሲ የሱን ፈለግ የተከተሉ እና በክፋት የተጨመቁ ባለስልጣናት እና በነፈሰበት የሚነፍሱ አጋሮቻቸው በኢትዮጵያ ሕዝብ ጫንቃ ላይ ተቀምጠው እየገደሉ እያሰሩ እያሳደዱ እና እየዘረፉ በመኖር ላይ ይገኛሉ ::እነዚህ አምባገነን የማፊያ ቡድን መንግስታዊ አሸባሪዎችን ከኢትዮጵያ ምድር ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ለማጥፋት ሁላችንም በጋራ ሆነን ከትግሉ ጋር ተቀላቅለን እጅ ለእጅ በመያያዝ በሃገር ውስጥ እና በዳር አገር የተጀመረውን ትግል ዳር በማድረስ ለድል በመብቃት ነጻነታችንን እና መብታችንን ማስከበር ይጠበቅብናል::የመለስ ዜናዊን የሙት መንፈስ እና የአምባገነን የወያኔ ጉጅሌዎችን ማጥፋት የምንችለው እያንዳንዳችን ስለ ነጻነታችን በምንከፍለው መስእዋትነት እና የዜግነት ግዴታ መሆኑን አንዘንጋ::‪#‎ምንሊክሳልሳዊ‬
- See more at: http://www.zehabesha.com/amharic/archives/45825#sthash.R5UsY9rB.dpuf

No comments:

Post a Comment