Friday, September 4, 2015

የተደበቀው የህወሓት ማንነት ከደደቢት እስከ ቤተ መንግስት ክፍል አምስት



የተደበቀው የህወሓት ማንነት ከደደቢት እስከ ቤተ መንግስት
ክፍል አምስት
==============================================
"...ሰፊው የትግራይ ህዝብ ስራ አጥቶ በሴተኛ አዳሪነትና ስደት ብቻ ሳይሆን በርሃብ፣ በድንቁርና እና በሽታ እየተሰቃየ በመኖሩ ምክኒያት ጠብመንጃ አንስተን በርሃ ለመውረድ ቻልን..."
ብሎን ነበር ህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ ያኔ በሽፍትነት ዘመኑ በ1968 ዓ.ም ባሳታመው የፖለቲካ ፕረሮግራሙ ከወደ ደደቢት፡፡
ህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ ይህን ካለ ከ40 ዓመታት በኋላ ዛሬም ረሃብ፣ በሽታ፣ ስራ አጥነት፣ ሴተኛ አዳሪነት፣ ድንቁርና እና ስደት አለ፡፡ እንዴውም ያን እሱ የተቸውን ዘመን በመሚያስመግን ሁኔታ፡፡ ታግየለታለሁ የሚለውን ትግራይን ጨምሮ መላው የኢትዮጵያ ወጣት በየቀኑ በግፍ ይሰደዳል፡፡
ስደትን አስቆማለሁ ብሎ ጠብመንጃ ያነሳው ህወሓት በስልጣን ዘመኑ ለዕልፍ አዕላፍ ኢትዮጵያዊያን ተሰዶ በባህር በዱር በገደልና በበርሃ ማለቅ ዋነኛ ምክኒያት ሆነ፡፡
ድህነትን ከአገራችን ምድር አጠፋለሁ ብሎ ታጥቆ የተነሳው ህወሓት ኢትዮጵያን ከኒጀር ቀጥላ የዓለም ሁለተኛዋ መናጢ ደሃ አገር ሆና በውርደት መዝገብ ስሟ እዲሰፍር አድርጎ ገናና ታሪኳን ሙልጭ አድርጎ ከምድረ ገፅ አጠፋው፡፡
ኮሌጅ የበጠሱ ወጣቶች የህወሓት ትምህርት ሜኒስቴር የሰጣቸው ክርታስ እንጀራ ሊያስቆርሳቸው ባለመቻሉ ረጅም የስደት ጅረት በመፍጠር ልክ እንደወንዞቻችን የተፈጥሮ ሀብታችንን ተሸክመው ያለማቋረጥ ወደ ውጭ መፍሰሳቸውን ቀጥለዋል፡፡ የመን ውስጥ ብቻ 800 ሺህ ወጣቶች እንደሚገኙ ዓለም አቀፍ የፍልሰት ድርጅት /I.O.M/ ያወጣው ሪፖርት ያረጋግጣል፡፡

Thursday, September 3, 2015

Wednesday, September 2, 2015

“የጦስ ዶሮ!” – ከኤርሚያስ ለገሰ

eprdfከኤርሚያስ ለገሰ በዛሬው እለት የአዲሳአባ ኢሕአዴግ ወደ 221 የሚጠጉ አመራሮችንና 4100 በላይ ሠራተኞችን ተጠያቂ ሊያደርግ እንደሆነ ተሰምቷል ። እነዚህ ሰዎች

የህወሀት የጥላቻ መርከብ በኢትዮጵያ እየሰመጠ ነው?

TPLF
ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም
ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ

የህወሀት የጥላቻ መርከብ በፍርሀት እና በጥልቅ የጥላቻ ውቅያኖስ ውስጥ ሰምጧልን?
እራሱን ህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ እያለ የሚጠራው ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ ገዥው ወንጀለኛ ድርጅት በኢትዮጵያ ውስጥ በማጭበርበር እራሱን መንግስት አስመስሎ ሆኖም ግን ትክክለኛ የመንግስት ባህሪያትን በምንም ዓይነት መልኩ ሳይላበስ እስከ አሁን ድረስ በመግዛት ላይ ይገኛል፡፡
በዚህ ባለፈው ግንቦት ወር ተካሄደ በተባለው የይስሙላ የቅርጫ ምርጫ የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ ይፋ በሆነ መልኩ 90 የፖለቲካ ፓርቲዎች ተመዝግበው በሚንቀሳቀሱበት የፖለቲካ ምህዳር ውስጥ ለዝንጀሮ/ጦጣው የይስሙላ ፓርላማ ከተያዙት 547 መቀመጫዎች ውስጥ እንደ ቀድሞው ለይስሙላ አንድ እንኳ መቀመጫ ለሌላ የተቃዋሚ ፖለቲካ ድርጅት ሳያቃምስ 547ቱንም መቀመጫዎች መቶ በመቶ ድል አሸነፍኩ ብሎ አለሃፍረት አወጀ፡፡

Ethiopia: The Military Member’s Message (Sadik Amhmed)

የመሐል ሀገር ሰው መልዕክት ለትግራይ ሰው! (በፍቃዱ ኃይሉ)

ማስታወሻ፡- ቀጥሎ የምታነቡት ጽሑፍ በፍቃዱ ኃይሉ ከቂሊንጦ እስር ቤት ለነገረ ኢትዮጵያ የላከው ነው፡፡
በፍቃዱ ኃይሉ
Fekadu Hailu zone9 blogger
ትግራይ የኢትዮጵያ ገናና ታሪክ መሬቷ ላይ የተጻፈባት ክልል ናት፡፡ ብዙዎች ‹‹የኢትዮጵያ ራስ ናት›› የሚሉት ለዚህ ነው፡፡ የኢትዮጵያን ታሪክ ወደኋላ 3000 ዓመት የሚያደርሰው የአክሱም ስልጣኔ አሻራውን ትቶ የሄደው በትግራይ ክልል፣ አክሱም ከተማ ነው፡፡ ከአረቦች ተቀድቷል የሚባለውን የንግስተ ሳባ ታሪክ ‹‹ክብረ ነገስት›› በሚባለው መጽሐፍ ተርጉመው ለዚህ ትውልድ ያኖሩልን የትግራይ ሊቃውንት ናቸው፡፡

ሌላው ቀርቶ ህብረ-ብሄራዊ ቅርስ የሆነንን የሳባ ፊደል ለመላው ኢትዮጵያዊ ያወረሱት የትግራይ ሊቃውንት ናቸው፡፡ ከኢትዮጵያዊነት ቀለሞች አንዱ የሆነው ያሬዳዊው ዜማ የተቀዳው ከትግራይ ምድር ነው፡፡ እነዚህና ሌሎች ያልጠቀስኳቸው እውነታዎች ሁሉም ኢትዮጵያዊ የሚኮራባቸው ናቸው፡፡
ኢትዮጵያዊነት በትግራይና በሌሎችም ህዝቦች አኩሪ ታሪክ፣ ባህል

የህወሀት የጥላቻ መርከብ በኢትዮጵያ እየሰመጠ ነው?

የህወሀት የጥላቻ መርከብ በኢትዮጵያ እየሰመጠ ነው?