Friday, September 29, 2017

የአርበኞች ማስታወሻ፣ (የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ ሬዲዮ)


መስከረም 19 ቀን 2010ዓ.ም
=======
በአርበኞች ግንቦት 7፣ ለአንድነትና ለዴሞክራሲ ንቅናቄ፣የተካሄደውን ጉባኤ አስመልክቶ አርበኛ ታጋይ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ የጉባኤው የመዝግያ ንግግር ያካተተ ጽሁፍ ይዘን ቀርበናል ዝግጅቱን እንዲከታተሉ በአክብሮት እጋብዛለሁ።

የአርበኞች ማስታወሻ፣ (የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ ሬዲዮ)

የዕለተ አርብ መስከረም 19 ቀን 2010ዓ.ም. ፕሮግራሞቻችን 
ዜና 
* የመስቀል በዓል በመላው አገሪቱ በሚገኙ የክርስትያን እማኞች ዘንድ ተከብሮ ዋለ 
* በኦሮሚያ ክልል ነገሌ ቦረና እሮብ ዕለት ወረቀት መበተኑን ተከትሎ ከፍተኛ ወጥረት መስፈኑ ተገለጸ.
* በባሌ ዞን ለተፈናቀሉ ከሶስት ሺ በላይ የሲዳማ ተወላጆች ድጋፍ እንዲደረግ ጥሪ ቀረበ
የሚሉትን ዜናዎችና
*የአርበኞች ማስታወሻ፣ በተሰኘው መሰናዷችን ትከታተሉት ዘንድ ግብዣችን ነው
http://www.patriotg7.org/ ላይ መከታተል የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡
Bilderesultat for professor berhanu nega

Thursday, September 28, 2017

ብርጋዴር ጄኔራል ኤፍሬም ባንጌ ከእስር ተለቀቁ (ኢሳት ዜና–መስከረም 18/2010)

Bilderesultat for ብርጋዴር ጄኔራል ኤፍሬም ባንጌ
በሌብነት ወንጀል ተጠርጥረው ከ2 መቶ ሚሊየን ብር በላይ በመንግስት ላይ ጉዳት አድርሰዋል በሚል ታስረው የነበሩት ብርጋዴር ጄኔራል ኤፍሬም ባንጌ ከእስር ተለቀቁ።
አቃቢ ሕግ ጄኔራል ኤፍሬም ባንጌ ኣንዲለቀቁ ያደረገው በሌሎች ተጠርጣሪዎች ላይ እመሰክራለሁ በማለታቸው እንደሆነ ጉዳዩን ለሚከታተለው ችሎት ገልጿል።
ጄኔራል ኤፍሬም ባንጌ በኦሞ ኩራዝ ቁጥር 5 የስኳር ፕሮጀክት ለዚሁ ተብሎ የተመደበውን በጀት ተቀናሽ በማድረግ ለግል ጥቅማቸው አውለዋል በሚል በሌብነት ተጠርጥረው መያዛቸው ይታወቃል።
ያጎደሉትም ከ2 መቶ 50 ሚሊየን ብር በላይ መሆኑ በወቅቱ ተነግሮ ነበር።
በዛሬው ችሎት ግን ጄኔራሉ በሌሎች ላይ ለመመስከር ፈቃደኛ በመሆናቸው ነጻ ተደርገዋል ተብሏል።
ፍርድ ቤቱም የጄኔራሉን በነጻ መለቀቅ አልተቃወመም።ጄኔራል ኤፍሬም ከኦህዴድ የተገኙ የኦሮሞ ተወላጅ ናቸው።
እርሳቸው በወቅቱ ሲታሰሩ ከሕወሃት ወገን በሌብነት የሚታወቁ ከፍተኛ ባለስልጣናት ሳይያዙ ለምን በኦህዴድ ላይ እስራቱ አነጣጠረ የሚል ጥያቄ ፈጥሮ ነበር።
ይህ በእንዲህ እንዳለ በቀድሞው በኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ዛይድ ወልደገብርኤል የክስ መዝገብ የኮሚኒኬሽን ሃላፊ በነበሩት አቶ ሳምሶን ወንድሙና ሌሎች 3 ተጠርጣሪዎች አቃቢ ሕግ ክስ መመስረት አለመቻሉ ተነግሯል።
እናም አቶ ካሳዬ ካቻ የተባሉና በዚሁ የክስ መዝገብ የተከሰሱ ግለሰብ በ20 ሺ ብር ዋስ ሲለቀቁ የአቶ ሳምሶን ወንድሙ ጉዳይና ሌሎች ተጠርጣሪዎች ለነገ ተቀጥረዋል።
በገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ሚኒስትር ዴኤታ አቶ አለማየሁ ጉጆ መዝገብ 16ኛ ተከሳሽ የነበሩት አቶ ኪዳን አባቡልቃም በነጻ ተሰናብተዋል።

(የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ ሬዲዮ)

አሁን የደረሰን ዜና ፡፡
የብአዴን የከፍተኛና የመካከለኛ አመራሮች ኮንፈረንስ ከተቀመጠለት ቀን ቀድሞ ዛሬ የተጠናቀቀ ሲሆን ፡ በአሁኑ ሰዓት ማዕከላዊ ኮሚቴዎች፡ የቤሮ ኃላፌዎችና ምክትሎች ፡ የየዞኑ ዋና እና ምክትል አስተዳደሪዎች ፡ የዋና ከተሞች ከንቲባና ምክትል ከንቲባዎች እንዲሁም የየዞኖች የብአዴን ተጠሪዎች በባህርዳር ከተማ ግራንድ ሆቴል አዳራሽ ዝግ ስብሰባ ተቀምጠዋል ፡፡
ግራንድ ሆቴል በአሁኑ ሰዓት ዙሪያውን በፌዴራል ፖሊሶች ጥብቅ ጥበቃ እየተደረገለት ሲሆን ማንም መውጣትም ሆነ መግባት አይችልም ፡ ምንጮች ስብሰባው በ2010 የድርጅት እቅድ ለመወያየት ነው ቢሉም እቅድን ሁሉም አባል እደሚወያይበት ተነግሮ ነበር አሁንም ለሌላ ቀን ቀጠሮ የተያዘለት ሆኖ እያለ በተናጥል መደረጉ አሳማኝ አይደለም ፡ ብአዴን በተመረጡ እና በተወሰኑ አመራሮች ላይ የእስር ውሳኔ ሊያሳልፍ ይችላል የሚል መረጃ እየመጣ ይገኛል በስብሰባውም ይህን ጉዳይ ይታያል ተብሎ ይጠበቃል።Image may contain: sky and outdoor

(የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ ሬዲዮ)

የዕለተ ሓሙስ መስከረም 18 ቀን 2010ዓ.ም. ፕሮግራሞቻችን 
ዜና 
* በሶማሌ ልዩ ሃይል ጥቃት የደረሰባቸው የኦሮሞ ተወላጆች ወደ ተለያዩ ሆስፒታሎች ተወስደው ህክምና እየተደረገላቸው መሆኑንና የሁለቱን ክልል መሪዎች ለማስማማት የሚደረገው ጥረት አለመሳካቱን 
* የባህርዳር ወጣቶች በመከላከያ አባላት እየተዋከቡ መሆኑን በምሬት መናገራቸው..
* በኦሮሚያ ቡሾፍቱ ከተማ በቅርቡ በሚከበረው የኤረቻ በዓል አንድም የታጠቀ ፖሊስ (ወታደር) እንደማይሰማራ የክልሉ መንግስት ማስታወቁ..
የሚሉትን ዜናዎችና
*የሃሳብ ጅረቶች በተሰኘው መሰናዷችን ትከታተሉት ዘንድ ግብዣችን ነው
http://www.patriotg7.org/ ላይ መከታተል የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡
Image may contain: sky and outdoor

Tuesday, September 26, 2017

Prof. Berhanu Nega speech at 2017 Patriotic Ginbot 7 convention - Asmara

እነሆ ደረሰ!!! ምኑ ትላላችሁ እንዴ? ጥቅምት 14 ነዋ የኢሳት 7ኛ ዓመት ክብረ-በዓል።

ይህንን አስመልክተን በኦስሎ ዕቱተን ስናደምቀው ልናመሽ ተዘጋጅተናል። ከእውቁ ጋዜጠኛ ፋሲል የኔ ዓለም እና እንዲሁም ቀናችንን በተስረቅራቂው ድምጿ ልታደምቀው ከስዊዲን በኪቤርድ ባለሙያው አርቲስት መርሶ ታጅባ ከዚህ በፊት ለህዝብ ባልተደመጡ ምርጥ ዝግጅቶቿ ስታስፈነድቀን ልታመሽ አርቲስት ሃኒሻ ሰለሞን ከለንደን እኛው ጋ ነች።
ኑ አብረን እንስራ አብረን እንደሰት። የኢትዮጵያ ሕዝብ ዐይንና ጆሮ ብቻ ሳይሆን እስትንፋስም የሆነውን ኢሳትን እንርዳ።ይህንን ስናደርግ በቅድሚያ የምንረዳው እኛኑ ራሳችንን ነው። በጋራ የምንሰራው ሁሌም የጋራ መሠረታችንን ነው።ለተወሰኑ ሰዎችና ድርጅቶች የሚተው ስራ አይደለም። የኢዮጵያውያንና የኢትዮጵያን ወዳጆች ሁሉ ወደዝግጅታችን ያመራሉ።
ቀኑ Oktober 14/2017 ከ15:ሰዓት ጀምሮ።
ቦታው John Collets plass 2
ወደ ሪክስ ሆስፒታል አቅጣጫ ሲጓዙ ከኡልቮል ሆስፒታል ቀጥሎ የሚገኘው የትሪክ መቆሚያ በስተቀኝ ያለው ባለ3 ፎቅ ህንፃ 2ኛው ፎቅ።
ይምጡ ይደሰቱ ኢሳትንም ይርዱ።
Image may contain: 2 people, people smiling, text

(የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ ሬዲዮ)


የዕለተ ማክሰኞ መስከረም 16 ቀን 2010ዓ.ም. ፕሮግራሞቻችን  ዜና 
* በምስራቅ ኢትዮጵያ በኦሮሞዎችና በኢትዮጵያ ሶማሌዎች ላይ የተፈጸመውን ግድያ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ንቅናቄ እና የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ መድረክ ማውገዛቸው 
* የኦሮሞ ተወላጆች የሚደርስባቸው ጥቃት አሁንም እንደቀጠለ መሆኑ
* የብሔረ አማራ ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ/ብአዴን/ማዕከላዊ ኮሚቴ መደበኛ ስብሰባ ያለስምምነት መበተኑ...
የሚሉትን ዜናዎችና 
*የሰባአዊ መብቶች ጥሰት በኢትዮጵያ በተሰኘው መሰናዷችን ትከታተሉት ዘንድ ግብዣችን ነው 
http://www.patriotg7.org/ ላይ መከታተል የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡Image may contain: sky and outdoor

Monday, September 25, 2017

Ethiopia: Security forces shot and injure several people in Debre Tabor ESAT News (September 25, 2017)

Several residents of Debre Tabor in Gondar who protested the detention of a church leader were shot and injured as security forces opened fire at an impromptu protest rally. Information reaching ESAT say several people including priests were also detained.
The priest, Aba Berhan, was arrested twice for protesting the installation of a telecommunication tower at the premise of his church.
Residents who heard the arrest of the priest for the second time were heading to their church with some carrying the cross when security forces opened fire.
ESAT sources say those who sustained injuries were admitted to the local hospital.
The sources also say the whereabout of the priest is not known.

ESAT DC Daily News Mon 25 Sept 2017

ESAT Daily News Amsterdam September 25,2017

የ2019 የአሜሪካ ዲቪ ሎተሪ በሚቀጥለው ሳምንት እንደሚጀምር ታወቀ። ብሪታኒያ፣ካናዳና ቻይናን ጨምሮ ከ20 የሚበልጡ ሀገራት ዜጎች በእድሉ እንዳይጠቀሙ ዕገዳ ተጥሏል። (ኢሳት ዜና–መስከረም 15/2010)

ብሪታኒያ፣ካናዳና ቻይናን ጨምሮ ከ20 የሚበልጡ ሀገራት ዜጎች በእድሉ እንዳይጠቀሙ ዕገዳ ተጥሏል። ፕሬዝዳንት ትራምፕ ወደ ስልጣን ከመጡ ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ ይፋ የሆነውና ከቀደመው የቀጠለው ፕሮግራም ከአፍሪካ ናይጄሪያን አስቀርቷል። እንደ ኢትዮጵያውያን አቆጣጠር መስከረም 23/2010 በዋሽንግተን ዲሲ ሰአት አቆጣጥር እኩለ ቀን ላይ የሚጀምረው ፕሮግራም እስከ ጥቅምት 28/2010 ድረስ እንደሚቀጥልም ታውቋል። በ2019 የዲቪ ሎተሪ የማይሳተፉ ወይንም ተቀባይነት የሌላቸው ሀገራትም ዝርዝር ይፋ ሆኗል። በዚህ ዕገዳ ውስጥ 50ሺህና ከዚያ በላይ ዜጎቻቸው በአሜሪካ የሚኖሩ ሀገራት በዲቪ ሎተሪው እንዳይሳተፉ ክልከላ ተደርጎባቸዋል። የካናዳ፣የቻይናና የብሪታኒያ ዜጎችም በክልከላው ውስጥ ተካተዋል።ከአፍሪካ ሀገራትም በዚህ አመት የዲቪ ሎተሪ ናይጄሪያውያን እንደማይሳተፉ ከወጣው ዝርዝር መረዳት ተችሏል። ከቻይና፣ብሪታኒያ፣ካናዳ፣ናይጄሪያና ባንግላዴሽ በተጨማሪ ብራዚል፣ኮሎምቢያ፣ዶሚኒካን ሪፐብሊክ፣ኤልሳልቫዶር፣ጓቲማላ፣ሔይቲ፣ሕንድ፣ጃማይካ።ሜክሲኮ፣ፓኪስታን፣ፊሊፒንስ፣ፔሩ፣ፖላንድ፣ደቡብ ኮሪያና ቬትናም በ2019ኙ የዲቪ ሎተሪ እንደማይሳተፉ የአሜሪካ መንግስት እገዳ ጥሏል። ሀገራቱ ባለፉት 5 አመታት ብቻ ከ50 ሺ ሰው በላይ በሕጋዊ መንገድ ወደ አሜሪካ በማስገባታቸው ከእድሉ መሰረዛቸው ተመልክቷል።Bilderesultat for የአሜሪካ ዲቪ ሎተሪ

H. RES. 128 “H. Res.128 - Supporting respect for human rights and encouraging inclusive governance in Ethiopia” በመባል የሚታወቀውና በኢትዮዽያ የሰብአዊ መብት እንዲከበር እንዲሁም ሁሉን አቀፍ መንግታዊ አስተዳደር እንዲመሠረት የሚጠይቀው ሕግ ሰኞ መስከረም 22, 2010 ለአሜሪካ ምክር ቤት ይቀርባል። ይህ ሕግ እንዲፀድቅ 202 224 3132 በመደወል (በሥራ ሠዓት ከ 9 a.m. እስከ 5 p.m. በ ዲሲ አቆጣጠር) ቀጥሎም 2 ቁጥርን በመጫን ከዛም የእርስዎን zip code በማስገባት የምክር ቤት ተወካይዎ ሕጉን እንዲደግፍ መጠየቅ ይችላሉ።

Ethiopia: Conference calls on regime to desist from instigating ethnic conflicts ESAT News (September 24, 2017)

A two day conference in Washington, DC that deliberated on building democratic institutions in Ethiopia demanded the regime to desist from hatching up conflict between ethnic groups in the country.
The conference that was held on Saturday and Sunday with the title “Ethiopia on a dangerous course” also deliberated on the critical issues in the country and called on all Ethiopians to “to resist the government’s ill-intentioned scheme of pitting one ethnic group against the other, stand shoulder to shoulder, and save their communities and country from the national calamity that is gradually unfolding.”
Speaking at the conference a representative of the Oromo Democratic Front, Dr. Mesfin Abdi called on all Ethiopians to unite against the divisive policies of the regime and work together to build a democratic Ethiopia.
Representatives of various political parties, civic organizations and activists took part at the conference and exchanged views on ways of defusing ethnic tensions instigated by the regime.
The conference also called upon the international community pressure the regime that is taking “the country on a dangerous path of destruction,” and said “financial assistance and military aid should only help promote the unity of the country, peace, development and encourage the rule of law in Ethiopia.Image may contain: one or more people and people on stage

Sunday, September 24, 2017

ESAT Special program, PG7 conference from Eritrea 24 Sunday 2017

የወደፊቱን መጠራጠርና መፍራት ካንዣበበብን አደጋ አያድነንም፤ መፍትሔው በቆራጥነት እውነታውን መጋፈጥና ትግላችንን ማጠናከር ብቻ ነው!!! (ከሰማያዊ ብሔራዊ ሸንጎ የተሰጠ መግለጫ)

ዛሬ በሀገራችን ከላያችን በተጫነው አገዛዝ ምክንያት በዜግነታችን እና በሉዓላዊነታችን ላይ ያልተጋረጠ የችግር ዓይነት የለም፡፡ የችግሩ ስፋትና ጥልቀት ከሀገር መፍረስ አደጋ ጀምሮ እስከ ዘር ፍጅትና የማያባራ የእርስ በእርስ ጦርነት ይደርሳል፡፡ በእነዚህ ችግሮች ፍርሃትና ጭንቀት ውስጥ ሆነን ምንም ሳናደርግ በየዕለቱ በአገዛዙ አረመኒያዊ ተግባር በዜጎች ላይ የተፈፀመው ግድያ፣የጅምላ እስር እና መፈናቀል በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ ጥልቅ ሀዘንና የልብ ስብራት ጥሎ አልፏል፡፡ ከላይ በጠቀስናቸው ውስብስብ ችግሮች ምክንያት እኛ ኢትዮጵያውያን ችግሮቻችንን በቅደም ተከተል አስቀምጦ መፍትሔከመፈለግ ይልቅ የመከራና የግፉ መብዛት የግልና የጋራ አስተሳሰባችንን ቆልፎ ምንም ነገር ወደ አለማድረግና መጭውን የመፍራት ለቁዘማ አስተሳሰብ የተዳረግን ይመስላል፡፡ ተስፋ ቢስነት፣አለመተማመን እና ስጋት የጋራ መገለጫዎቻችን እየሆኑ መጥተዋል፡፡
Image may contain: 2 people
 
Image may contain: 14 people, people sitting
የጨቋኞቹ ሃላፊነት የጎደለው ተግባር ሀገርን እስከማፍረስ የደረሰ ከመሆኑም በተጨማሪ የአገዛዙ መፍረስ እውን መሆኑን የተረዳን የተደራጀንም ሆነ ያልተደራጀን የፖለቲካ ኃይሎችም ብንሆን "ለውጡን የመሸከምና የመምራት አቅም የለንም" በሚል የመንፈስ ድካም የለውጡን አይቀሬነት ውስጣችን እያመነ ለውጡን በፍርሃት እንድንጠብቀው ተገደናል፡፡ በመሆኑም ይህ አመለካከታችን አውቀነውም ይሁን ሳናውቀው ለአገዛዙ እድሜ መራዘም አወንታዊ አስተዋፅዖ ከማድረጉም በተጨማሪ ባይቀሬው ለውጥ ኢትዮጵያ ወደ ዴሞክራሲ የመሸጋገሯን ተስፋ በማመንመን የምንፈራውን መራራ ፅዋ እንድንጎነጭ ያደርገናል፡፡ 

(የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ ሬዲዮ)


የዕለተ እሁድ መስከረም 14 ቀን 2010ዓ.ም. ፕሮግራሞቻችን 
ዜና 
* በኦሮሚያ እና ሶማሌ ክልል ድበር ላይ ተኩስ እንደነበረ መገለጹ 
እንዲሁም ተፈናቃዎች ወደ ተወለዱበት አካባቢ እንዲሄዱ መገደዳቸው
* በደረጃ *ለ* ነጋዴዎች የተጣለባቸውን ግብር እንደማይከፍሉ ማስታወቃቸው
* ሰላማዊ ሰልፍ በተለያዩ የአውሮፓና የሰሜን አሜሪካ ከተሞች መካሄዱ 
የሚሉትን ዜናዎችና 
*የማህበራዊ መገናኛ ብዙሃን ዳሰሳ በተሰኘው መሰናዷችን ትከታተሉት ዘንድ ግብዣችን ነው 
http://www.patriotg7.org/ ላይ መከታተል የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡

Saturday, September 23, 2017

Ethiopia: Conference on building democratic institution kicks off in DC H. Res. 128 to be presented before U.S. Congress for vote ESAT News (September 23, 2017)

A two day conference on “building democratic institutions in Ethiopia” kicked off today in Washington, DC where scholars from a spectrum of professions will discuss on study papers on issues such as U.S. policy towards the Horn of Africa, the role of Diaspora in building democracy in Ethiopia as well as corruption, public trust and economic development among others.
One of the topics for Saturday’s session was H. Res. 128, a bill by the U.S.Congress on “supporting respect on human rights and encouraging inclusive governance in Ethiopia,” which will be tabled for vote before the House of Representatives on October 2, 2017.
One of the sponsors of the bill, Congressman Mike Coffman, Representative for Colorado's 6th district, in a message to the conference said H. Res. 128, which will be tabled to congress next Monday will be instrumental in taking specific steps by the U.S. in improving human rights and democracy in Ethiopia.

Friday, September 22, 2017

Tensae Radio Sept 22 2017

Ye Tewodros Raey Theatre in Oslo Advert

የህወሃት የስለላ ሃላፊዎች ፖለቲከኞቻቸውን አስጠነቀቁ (ኢሳት ዜና መስከረም 12 ቀን 2010 ዓም)


የህወሃት የደህንነት ባለስልጣናት (intelligence officers) በአገሪቱ በተለይም በምስራቅ ኢትዮጵያ ያለው ሁኔታ አደገኛ እና አስፈሪ ነው ሲሉ የድርጅቱን መሪዎች አስጠንቅቀዋል። በሶማሊ ልዩ ሃይል ላይ ያላቸውን ግምገማም አስቀምጠዋል።
ምንጮች እንደገለጹት በምስራቅ ኢትዮጵያ በሶማሊያና በሶማሊላንድ የተደራጁ ታጣቂዎች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተጠናከሩና ጉልበት እያገኙ መምጣታቸውን የደህንነት አባላቱ ገልጸዋል። (ምስል ከፋይል)Bilderesultat for የሶማሊ ልዩ ሃይል
አካባቢውን ያረጋጋል በሚል በመከላከያና በክልሉ መስተዳደር በጥምረት የተቋቋመው የሶማሊ ልዩ ሃይል በማንኛውም ጊዜ ሊከዳና ጠንካራ ውጊያ ከገጠመው በቀላሉ የሚሸሽ በመሆኑ ህወሃት በዚህ ሃይል ላይ የሚያሳየውን መተማመን እንደቀንስ የደህንነት ሃይሎች ለአመራሮች ነግረዋል። 
ከሁለት ሳምንት በፊት ከደቡብ ምዕራብ ሶማሊያ በፑንትላንድ በኩል የገቡ፣ የኢትዮጵያን ወታደሮች ዩኒፎርም የለበሱ ማንነታቸው ያልታወቀ ታጣቂዎች በሶማሊ ልዩ ሃይል ላይ በፈጸሙት ጥቃት 36 የልዩ ሃይል አባላት መገደላቸውን የደህንነት ሃላፊዎች ለአመራሮቹ ነግረዋል። እንዲሁም ከሁለት ወራት በፊት 11 የልዩ ሃይል ሃይል አባላት በተመሳሳይ ቦታ ላይ መገደላቸውና አንድ መኪና መቀማታቸው የደህንነት አባላቱ በሶማሊ ልዩ ሃይል ላይ ያላቸው እምነት እንዲቀንስ አድርጎታል። 

09/18/17 ሰላም ለነጻነት አፍቃሪዎች ሁሉ እየተመኘሁ ከዚህ ቀጥዬ በአስመራ ስለነበረኝን ቆይታ ስሜቴን ለመግለጽና የተሰማኝን ለማካፈል ያህል ወደመጣሁበት ስመለስ መንገድ ላይ (በአይሮፕላን ውስጥ) የጻፍኩትን እንደ ልምድ ያለው ጸሃፊ ጽሁፍ ሳይሆን ስሜቱን ለመግለጽ እንደሞከረ አንድ ተራ ሰውና የግል አስተያየት ተረዱልኝ።

የአግ7 አንደኛ አጠቃላይ ጉባኤ ኤርትራ ውስጥ እንደሚደረግ ስሰማ እዛ ያሉትን ጓዶቻችንን በአካል ማግኘትና ስላለውም አጠቃላይ ሁኔታ በቅርበት ለማየት እድል ስለሚፈጥር ደስታ ተሰማኝ ለመሄድም አሰብኩ ነገር ግን እድሉን ማግኘት በመፈለግ ብቻ የሚሆን ስላልነበረና ለመሄድ የሚያስፈልጉትን መስፈርቶች ማሟላት ብቻ ሳይሆን መሄድ የሚፈልገው ከተሰጠን ኮታ በላይ ስለነበረ ውድድርም ይጠበቅብን ነበር፤ ለማንኛውም በመመሪያውም መሰረት የተጠየቀውን በማሟላቴና ለመሄድም ለውድድር ቀርበን ከሌሎች ጓዶቼ ጋር ስለተመረጥኩ ለመሄድ ዝግጅት ጀመርን በዚሁ አጋጣሚ የነበረው አጭር ግዜም ቢሆን በአስቸኳይ የድርጅታችን አባላቶች በመነጋገር ለዳር አገር ላሉት ጓዶቻችን የሚሆኑ ነገሮችን ለመግዛት የሚያስችል ገንዘብ በማዋጣት፣ የማህበረ ኢትዮጽያ (የዲሲ ግብረ ሃይል) አባላትም የአቅማቸውን ገንዘብ በመስጠት እንዱሁም መሄዳችንን የሰሙ አገር ወዳዶች ይጠቅማል ያሉትን ሁሉ በመስጠት ላሳዩት ጓዳዊ ድጋፍ አርእያነታቸውን ሳላመሰግን አላልፍም። ወደ መንገዴ ልመለስና ለመሄድ እየተዘጋጀን እያለ ወሎ ሰፈር በመባል የሚታወቅ የፌስ ቡክ ገፅ የጉባዬተኞችን ስም ዝርዝር በሁለት ዙር በማውጣት ለማስፈራራት ይሁን መረጃ ይደርሰኛል ለማለት ፈልጎ ወይም ስማችንን በመለጠፉ ፈርተው ይቀራሉ ብለው አስበው ይሁን ባይገባኝም የለጠፉትን አይተንላቸው ነበር፤ እኛን ግን እንኳን ሃሳባችንን ሊያስቀይር ይቅርና እንደውም በእልህ ለመሄድ ተወዳዳሪዎችን አበዛብን እኔንም ስሜን አሳስተው በመፃፋቸው ቅር አሰኙኝ። ለማንኛውም ትግሉ ብዙ የሚጠይቅ መሆኑን አውቀን የገባንበት ስለሆነና ወያኔም የሚችለውን ሁሉ ከማድረግ ወደኋላ እንደማይል ስለምንረዳ እነሱ በሚሰሩት ስራ የሚደናገጥ ሳይሆን የቆረጠና የማይፈራ የሚሰራውን ስራ ለምን እንደሚሰራ ጠንቅቆ የተረዳ አባላት ያሉት ድርጅት ውስጥ በመሳተፌ ደስ እያለኝ ዝግጅታችንን አጠናቀን ጉዟችንን ወደ ዳር አገር ለማቅናት(Sep 1st) ከወዳጅ ዘመድ ተሰነባብተን ከጓዶቼ ጋር በተቀጣርንበት ቦታ በግዜ ብንገኝም የያዝነው ቫን መኪና እቃ ከአሰብነው በላይ በመብዛቱና ሁሉንም መያዝ ባለመቻሉ መኪና መቀየር ግድ ሆነብን ወቅቱም የ (Labor Day) ሳምንት ስለነበር ሌላ መኪና ለማግኘት ትንሽ ግዜ ቢወስድብንም የምንፈልገውን ግን አገኘን፤ በቂ ግዜም ስለነበረን እንደርሳለን ብለን ጉዟችንን መነሻችን ወደሆነው የኒዮርኩ (JFK) አይሮፕላን ማረፊያ አደረግን ነገር ግን ለመሄድ እንደነበረን ጉጉት መንገዱ አልተባበረንም ነበርና በሰአቱ መድረስ አልቻልንም ነበር፤ በእለቱም ሌላ የነበረን አማራጭ ስለሌለ አድረን በቀጣዩ ቀን መንገዳችንን ለመሞከር እዛው ማደር ስለነበረብን በአካባቢው የሚገኙ ቤተሰቦቼ ጋር ለመሄድ መንገድ ስንጀምር በደህና ደረሳችሁ ለማለት ለአንደኛው ጓዳችን ባለቤቱ ስልክ ስትደውልለትና የሆነውን ሲያስረዳት የሰማ ሌላኛው ጓዳችን አንድ ቀልድ ልንግራችሁ ብሎ የነገረን ቀልድ ንዴታችንን አጥፍታ እየተሳሳቅን የምንሄድበት አደረሰን። ምን አለን መሰላችሁ " አንዲት የቅንቡርስ ባለቤት ባሏ ዘመቻ ሊሄድ ሲነሳ ድግስ ደግሳ ዘመድ ወዳጆቻቸውን ጠርታ በትልቁ ስንብት ተደርጎለት ይለያያሉ ባለቤትም ብቻዋን እንዳትሆን ዘመዶቿ ጋር ቆይታ ስትመጣ ዘማቹ ባለቤቷን ከሩቅ እቤታቸው ውስጥ ታየውና በድል ተመለሰ ብላ እልልታዋን ስትለቀው ባለቤቷም ኧረ ዝምበይ ዝምበይ ገና መቼ ሄድኩና አላት እሱ ለካ እዚያው ሲርመጠመጥ ቆይቶ ነበር ሲለን ከኛ ሁኔታ ጋር ስለተገጣጠመብን በጣም ነበር ያሳቀን" ለማንኛውም እንዲህ እንዲህ እያልን ደርሰን ግዚያችንን ከቤተሰብ ጋር አሳልፈን በንጋታው በድጋሚ እንዳያመልጠን በግዜ ወደ ኤርፓርት ሄደን ቅጣታችንን ተቀብለን ጉዞ ወደ ካይሮ አደረግን፤ ካይሮ ስንደርስ ወደ ኤርትራ የሚወስደንን አይሮፕላን ለመያዝ 12 ሰአት መጠበቅ ነበረብን ስለዚህ ሁሉ ለበጎ ነው እንዲሉ ፒራሚድን፣ የአባይ ወንዝን፣ ጣህሪር አደባባይን (Tahrir Square) ጨምሮ የተለያየ ቦታዎችን ጎብኝተን ያላሰብነውን አይተን ሰአታችን ሲደርስ ጉዞ ወደ መድረሻችን ወደሆነችው ኤርትራ ጀመርን፤ መድረስም አይቀር ከቤት ከወጣን በ4ተኛ ቀናችን በማታ አስመራ ደረስን።

Warm reception for Prof Berhanu Nega, Patriotic Ginbot 7 Chairman in Fr...

የአርበኞች ግንቦት 7 በጎንደር አካባቢዎች እየተንቀሳቀሰ ነው ሲል አቃቢ ህግ ማስታወቁ (የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ ሬዲዮ)


የዕለተ አርብ መስከረም 12 ቀን 2010ዓ.ም. ፕሮግራሞቻችን 
ዜና 
* በደቡብና ኦሮሚያ ድንበር አካባቢ በተነሳው ግጭት የሞቱ ሰዎች ቁጥር ከ45 በላይ መድረሱ 
* የፀጥታ አካላት በዝርፊያ ላይ ተሰማርተዋል ሲሉ ነዋሪዎች ማማረራቸው 
የሚሉትን ዜናዎችና 
*ይድረስ ለአጋዚው ወንድሜ የተሰኘ ደብዳቤ የአርበኞች ማስታወሻ በተሰኘው መሰናዷችን ይቀርባት ትከታተሉት ዘንድ ግብዣችን ነው 
www.patriotg7.org ላይ መከታተል የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡

Thursday, September 21, 2017

Ethiopia’s refugees unsafe in Kenya and elsewhere: Human Rights Watch ESAT News (September 21, 2017)

Human Rights Watch said it has documented numerous cases of harassment and threats against Ethiopian asylum seekers in Kenya and elsewhere since 2010.
Horn of Africa senior researcher for the watchdog group, Felix Horne, wrote in a report titled “The Long Arm of Ethiopia Reaches for Those Who Fled,” that Ethiopian asylum seekers were “assaulted, detained, and interrogated before Ethiopian officials in Nairobi, and forced to return to Ethiopia. Many also received threatening phone calls and text messages from Kenyan and Ethiopian phone numbers.

ስራ የፈታ አይምሮ የዝግቱ መጠን ከብረት ይልቃል!! (ከአርበኞች መንደር አርበኛ ታጋይ አምደማሪያም እዝራ)


ያላችሁትን በሉ እኛ በብርቱ ስራ ተጠምደናል!! የስራችንም ውጤት ነገ ታዩት አላችሁ!! ያኔ…የእኛ ውጤት ለእኛ ብቻ ሳይሆን ለእናተም ይበቃል!! ድፍን ኢትዮጵያን ያዳርሳል!! እመነኝ ጽፈኛ፥ እመነኝ ዘረኛ፥ እመነኝ የበግ ለምድ ደራቢ ተኩላ!!…የተዋረስከው እኩይ ዓላማ እውን አይሆንም!! በአይንህ በብረቱ እያየኸው እንደ ጉም ይተናል!!
ኢትዮጵያ አንድናት!!
ኢትዮጵያ አባሻ አይደለችም ማንም እንደ ፈለገ የሚፈትታት!!
የተመሰረተች እንጂ በደምና በአጥንት!!

Image may contain: 1 person, closeup

(የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ ሬዲዮ)


መስከረም 11 ቀን 2010 ዓ.ም.ዜናዎች
* ከሶማሌ አሁንም የኦሮሞ ተወላጆች እየተፈናቀሉ መሆናቸው።
* ከቅማንት ጥያቄ ጋር በተያያዘ ድምጽ በተሰጠ ማግስት ሶስት ሰዎች መገደላቸው።
* የኢትዮጵያን የሰብአዊ መብት ሁኔታ የሚመለከተውን ረቂቅ የአሜሪካ ምክር ቤት እንዲያጸድቀው መጠየቃቸው። 
የሀሳብ ጅረቶች፣ በአርበኛ ታጋይ ሜሮን አለማየሁ
የሚሉትን ዜናዎችና ሙሉ ፕሮግራሞቻችንን በ http://www.patriotg7.org/ ላይ መከታተል የምትችሉ መሆኑን በአክብሮት እንገልፃለን፡፡Image may contain: sky and outdoor

Efeta September 20 2017

ESAT Zare with Kassahun Yilma 19 Sep 2017

Wednesday, September 20, 2017

Ye Tewodros Raye Theatre in Bergen Advert

ድምፃዊ ሻምበል በላይነህ ከኤርትራ

በኢትዮጵያ ውስጥ በሚካሄደው ሌብነት በግንባር ቀደምትነት ሲጠቀሱ የነበሩትና ከሀገር እንዳይወጡ እገዳ ተጥሎባቸው የቆየው አቶ አባይ ጸሀዬ ለሕክምና ከሀገር መውጣታቸውን ምንጮች ለኢሳት ገለጹ። (ኢሳት ዜና–መስከረም 10/2010)

 ይህ በእንዲህ እንዳለ ራሳቸውን በኮሚቴ ያደራጁ የትግራይ ምሁራንና የሀገር ሽማግሌዎች በሌብነት ላይ የተጀመረው ዘመቻ እንዲቆምና የታሰሩትም እንዲፈቱ መጠየቃቸው ተሰምቷል። በኢትዮጵያ ውስጥ በሚካሄደው ሌብነት በግንባር ቀደምትነት የሚጠቀሱት አቶ አባይ ጸሃዬ ናቸው። ይህን ተከትሎም ከሀገር እንዳይወጡ እገዳ ተጥሎባቸው መቆየቱም የሚታወስ ነው። ሌቦችን የማደኑ ስራ እየተካሄደ ነው በሚባልበት በአሁኑ ሰአት ደግሞ ራሳቸውን በኮሚቴ ያደራጁ የትግራይ ምሁራንና የሀገር ሽማግሌዎች በሌብነት ላይ የተጀመረው ዘመቻ እንዲቆምና የታሰሩትም እንዲፈቱ በመጠየቅ ላይ መሆናቸውም ተሰምቷል።Bilderesultat for አቶ አባይ ጸሃዬ እነዚህ በኮሚቴ ተደራጁ የተባሉት የትግራይ ምሁራንና የሀገር ሽማግሌዎች ባሳደሩት ተጽእኖም አቶ አባይ ጸሀዬ ለሕክምና ከሀገር እንዲወጡ ተደርጓል ሲሉ የኢሳት ምንጮች ገልጸዋል። ባለትዳርና የልጆች እናት ከሆኑት ወይዘሮ ሳሌም ከበደ ጋር በአንድ ጣራ ስር መኖራቸው የተገለጸው አቶ አባይ ጸሀዬ ወይዘሮ ሳሌም ከበደ ከታሰሩ በኋላ በምርመራ እየወጡ ያሉ የወንጀል ድርጊቶቻቸው እንዲሁም ባለቤታቸውን መታደግ አለመቻላቸው በፈጠረባቸው ውጥረት መታመማቸውን ምንጮች ገልጸዋል። ራሳቸውን በኮሚቴ ያዋቀሩት የትግራይ ምሁራንና የሀገር ሽማግሌዎች አቶ አባይ ጸሃዬ በሕወሃት ትግል ውስጥ በመሪነት ጭምር የተጫወቱትን ሚና በመዘርዘር እንዳይታሰሩ ሲማጸኑ መቆየታቸውም ተመልክቷል። ይህ ርምጃ በሕዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ ውስጥ ያለውን ችግር ያባብሳል፣ለጠላትም በር ይከፍታል በሚል የጸረ ሌብነት ዘመቻው እንዲቆም ሲወተውቱ መቆየታቸውም ተሰምቷል። የታሰሩትም ይቅርታ ጠይቀው በማስጠንቀቂያ እንዲፈቱም ተማጽኖ ማቅረባቸው ታውቋል።–የታሰሩትን ለመፍታት ስለመወሰኑ የታወቀ ነገር ባይኖርም እንኳን። ህኖም ክትትል ሲደረግባቸው የነበሩትና ይታሰራሉ ተብለው የሚጠበቁት ባለስልጣናትና ነጋዴዎች የሚደረግባቸው ክትትል መቆሙን እነዚሁ ምንጮች ገልጸዋል። በሀገሪቱ በሚፈጸመው ሌብነት ፊታውራሪ ተብለው የሚጠቀሱት አቶ አባይ ጸሃዬ ለሕክምና እንዲሄዱ የተፈቀደው በሌብነት ላይ የተጀመረው ዘመቻ በመቆሙና ከትግራይ ሽማግሌዎች ተጽእኖ ጋር በተያያዘ እንደሆነም መረዳት ተችሏል። አቶ አባይ ጸሃዬ ለህክምና የወጡት ወደ ጀርመን እንደሆነ ቢገለጽም በትክክል ወደየትኛው ሀገርና የህክምና ማዕከል እንደሄዱ ግን ማወቅ አልተቻለም።

Professor Haile Larebo on Historical Distortions

በአዲስ አበባ የመብራትና የውሃ ችግር መባባሱ ተገለጸ (ኢሳት ዜና–መስከረም 9/2010)

በአዲስ አበባ የመብራትና የውሃ ችግር መባባሱ ተገለጸ።
በአብዛኛው የከተማዋ አካባቢዎች ውሃ ከጠፋ ቀናት መቆጠራቸውን ነዋሪዎች ገልጸዋል።
ከፍተኛ የሆነ የመብራት መቆራረጥ መኖሩ ደግሞ ነዋሪዎቹን ለከፋ ችግር መዳረጉን ለማወቅ ተችሏል።

ከእነዚህ በተጨማሪ የነዳጅና የስኳር እጥረትም በከተማዋ በመከሰቱ ለከፍተኛ ችግር መጋለጣቸውን ነዋሪዎች በምሬት እየተናገሩ ነው።
በሌላ በኩል መንግስት ወደ ውጭ ስኳር በመላክ የውጭ ምንዛሪ ለማግኘት እየሰራ መሆኑን ከገለጸ ከቀናት በኋላ 7ሚሊዮን ኩንታል ስኳር ከውጭ ለማስገባት ዝግጅት እየተደረገ ነው ሲል ትላንት ማስታወቁ ሌላ ጥያቄን ፈጥሯል።
ኢትዮጵያ በድርቅ በተመታችበት በዚህን ወቅት ለኬኒያ በቆሎ መሸጧን የኬኒያ ንግድ ሚኒስቴር ገልጸዋል።

ለአዲስ አበባ ነዋሪዎች ሁሉ ነገር ችግር ሆኖባቸዋል። የስልክ ኔትወርክ የለም። ስኳር ጠፍቷል። ውሃ ለቀናትና አንዳንድ ጊዜም ከሳምንት በላይ አያገኙም። የመብራት መቆራረጥም ሌላውና ከፍተኛው ችግር ነው። የነዳጅ እጥረትም ለነዋሪው ብርቱ ፈተናን መደቀኑ ነው የተሰማው።Bilderesultat for አዲስ አበባ
የውጭ ምንዛሪ የለም። የንግድ እንቅስቃሴው ተዳክሟል። ችግሩ ከዕለት ወደ ዕለት እየተባባሰ ነው ተብሏል።

Tuesday, September 19, 2017

Ethiopia-እልቂት ያስከተለዉ የኦሮሞና ሶማሌ ግጭት በቋንቋ የተመሰረተዉ የ-ፌደራል የ-አከላለል ችግር ይሆን መ...

Over 70,000 displaced, killings continue in Eastern Ethiopia ESAT News (September 19, 2017)

The ethnic violence in Eastern Ethiopia continued with new reports showing further killings and the displacement of over 70,000 people.
Ethiopia’s government spokesperson, Negeri Lencho, confirmed the number of the displaced to China's Xinhua news agency and said the hot spot areas are now being manned by regime’s army and the situation has calmed down. Separate reports coming out of the region however show that fighting has still continued on Tuesday resulting in the death of several people.
There has been a long standing turf dispute between the Somali and Oromo communities in Eastern Ethiopia with the regime being accused of arming both sides and not intervening in time once the killings began.
There have also been reports of fighting between two clans with in the Somali community in Chinaksen in which 5 people were killed and 6 injured. The reports also say the Somali Special Police Force, which is said to be controlled by the TPLF, had been involved in the deadly clashes between the Geri and Jarso clans.
Reports also show that fighting broke out between the Somali Region Special Police and the Guji in Bale. Several people are feared dead.
On Monday, a truck carrying the displaced from the Somali region and heading to Harar overturned killing 6 people and sending 3 others to the hospital.

በኢትዮጵያ በየቦታው እየተከሰቱ ያሉ ችግሮችና የተከተለው ቀውስ ምክንያቱ ሕወሃት በመሆኑ ሊወገድ ይገባል ተባለ (ኢሳት ዜና–መስከረም 9/2010)

 በኢትዮጵያ በየቦታው እየተከሰቱ ያሉ ችግሮችና የተከተለው ቀውስ ምክንያቱ ሕወሃት በመሆኑ ይህን ቡድን ከማስወገድ ውጭ መፍትሄ እንደማይኖር አርበኞች ግንቦት 7 አስታወቀ።
የሕወሃት የስልጣን ዘመን እያበቃ ባለበት በአሁኑ ወቅት በኦህዴድና ብአዴን ውስጥ ያሉ እውነታውን የተገነዘቡ ወገኖች በመጨረሻው ሰአት ራሳቸውን ከተጠያቂነት ነጻ የሚያደርግ ስራ እንዲሰሩም አርበኞች ግንቦት 7 ጥሪ አቅርቧል።
የወቅቱን የኢትዮጵያ ሁኔታ በማስመልከት አርበኞች ግንቦት 7 በሳምንቱ መጨረሻ ባወጣው በዚህ መግለጫ የኦሮሚያና የሶማሌ ክልል አዋሳኝን መሰረት አድርጎ እየተከተለ ያለው ግድያና መፈናቀል አሳሳቢ እንደሆነ በመጥቀስ ድርጊቱ ግን ስልጣን ላይ ያለው ቡድን ባስታጠቃቸው ሃይሎች የሚከወን መሆኑን አመልክቷል።
መታወቂያ እየተጠየቁና ብሔር እየታየ የተፈጸመው ድርጊት ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ አስደንጋጭ የማስጠንቀቂያ ደወል መሆኑንም በመግለጫው አስፍሯል።
በዚያው በምስራቅ ኢትዮጵያ በሀረሪ ክልላዊ መንግስት ውስጥ የተከሰተው ሁኔታ አሳሳቢና ለነዋሪው አደጋ የደቀነ መሆኑን የዘረዘረው መግለጫ ህወሃት በሰሜን ኢትዮጵያ ጎንደር ውስጥ በጭልጋ፣በመተማና በሽንፋ ከፍተኛ የሰራዊት ሃይል ማስፈሩንና ይህ ሃይል በሕዝብ ላይ ጥቃት ለመክፈት የተዘጋጀና ትዕዛዝ የሚጠብቅ እንደሆነም ገልጿል።
በጠገዴ አካባቢ በሕወሃትና ብአዴን መካከል የተደረገው ስምምነት ብአዴኖች የሕወሃት አገልጋይነታቸውን ይበልጥ ያረጋገጡበት እንደሆነ መግለጫው አስታውሷል።
ሰሜን ጎንደርን በሶስት ለመክፈል የተያዘው እቅድ የደቀነውንም አደጋ አመልክቷል።

በአካባቢው እየተወሰደ ያለው ርምጃ ሕወሃት አማራን በአጠቃላይ ጎንደርን በተለይ ለማዳከም ዘርፈ ብዙ ፕሮጀክቶችን ዘርግቶ በመንቀሳቀስ ላይ መሆኑን እንደሚያሳይም መግለጫው አስታውቋል።
በአጠቃላይ በሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች እየተከሰቱ ያሉ ቀውሶች ሕወሃት ሰራሾች በመሆናቸው ሕወሃት ሳይወገድ መፍትሄ እንደማያገኙ አርበኞች ግንቦት 7 አስታውቋል።
በመላው የኢትዮጵያ ክፍል ከሕዝብ ጋር ሆኖ ጸረ ሕወሃት የሕዝብ ትግል እያስተባበረ መሆኑንም በመግለጽ ትግሉ ፍሬ እንደሚያፈራም ጥርጥር እንደሌለው አመልክቷል።ለተቃዋሚ ሃይላትም የትብብር ጥሪ አቅርቧል።

ESAT Daily News Amsterdam September 19,2017

ኢሳት መረጃ

በሰሜን ጎንደር ከጎንደር አዘዞ እስከ መተማ ድረስ ባለው መስመር 180 ኪ.ሜ ጨምሮ በውስጥ ዙሪያ ቀበሌወች እና መንደሮች ውጥረቱ ጨምሯል የተኩስ ድምፆች ይሰማሉ። በጭልጋ ወደ ሸዲ በሚወስደው መንገድ ነጋዴ ባህር ሳይደርስ ግንት ከተራራው የአጋዚ ጦር ሰፍሯል። በሸዲ ጎንደር በር ባለው ወታደራዊ ካምፕ በተጨማሪ በቅርብ ርቀት ባለችው ብርሺኝ ገንዳውሃ አካባቢ የጦርነት ቀጠና መስሏል።ከሸዲ ሽንፋ መንገዱ በከፊል ተዘግቷል። ከሸዲ መተማ 37 ኪ.ሜ በመሃል ያለችውን ኮኪት ከተማን ጨምሮ ከፍተኛ ውጥረት አለ። መንገዶች ዝግ ናቸው።

የራሱን እሳት በእሳት ማጥፋት የተካነበት 'ጥበበኛው' ህወሓት 9ካሳሁን ይልማ)

ለህወሓት የኦሮሞ-ሶማሌ እና የአማራ-ቅማንት ጉዳይ ልክ እንደ እሳት አደጋ ውህ ማጥፊያ ናቸው። በነሱ ሞት ራሱን ከሞት ያስነሳል። በነሱ እሳት የራሱን እሳት ያጠፋል። ነገሮችን ወደኋላ መለስ ብለን ለማሰላሰል ጊዜ ካለን:- ተቃዋሚዎች ጠንካራ ሆነው ሰላማዊ ሰልፎች በየቦታው ሲቀጣጠሉና ሕዝቡ መሰረታዊ ጥያቄዎቹን አንግቦ በድፍረት አደባባይ መውጣት ሲጀመሩ የህወሓት የመጀመርያ እርምጃ የተቃዋሚ አመራሮችን ማሰር ነው።መንግስትን የሚነቀንቅ ጥያቄ ያነሳው ሕዝብ ወዲያውኑ በሚያስገርም ፍጥነት ዋና አጀንዳውን ጥሎ መሪዎቼ ይፈቱ FREE እከሌ በሚል ዘመቻ ይጠመዳል። ይህ ሂደት ከ2 እና 3 ዓመታት በላይ በሚካሄዱ የፍርድቤት ምልልሶች ታጅቦ ይቀጥላል። ከዚያ መንግስት በይቅርታና ምህረት በሚል ታፔላ አመራሮቹን ዝቅ አድርጎ ይፈታቸዋል። ከዚያ ሕዝቡ በመሪዎቹ መፈታት ይደሰታል። አበቃ።
እናም ገዢው ሥርዓት የሚፈልገውን አጀንዳ በቅዱ መሰረት እያስኬደ ነው። ስጋት ሆኖ ህወሓትን እንቅልፍ የነሳው የኦሮሞ ተቃውሞ ሰደድ ተዳፍኗል። ኦሮሞ ያቀጣጠለውን እሳት አጥፍቶ ራሱን ሊያቃጥል የመጣ እሳት እያጠፋ ነው፣ ለዚያውም ኦህዴድን እየተማጸነ። ኦህዴድ ደግሞ ያው አለቃው ዘንድ ደጅ ይጠናል።Image may contain: 1 person, sitting, beard and indoor
አማራና ቅማንት ሪፈረንደም - ሕዝበ ውሳኔ ተብሎ በውጤቱም "ድሉ የሕዝብ ሆኗል" እየተባለ ባለበት ሰዓት ዛሬ 4 ሰዎች መገደላቸውን ሰምተናል። ጨቋኝ ስርዓት ባለበት ቦታ ሕዝበ ውሳኔ ይተገበራል ብሎ ጮቤ መርገጥ በራሱ የዋህነት ነው። 26 ዓመታት በሙሉ ደግመን-ደጋግመን የምናውቀው ከፋፋይ አረመኔ ገዢ የሕዝብ ምርጫ ይመቸዋል ብለን ካሰብን ስርዓቱ ቅቡል ነው ብለን እያመንን ነው።

(የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ ሬዲዮ)


መስከረም 09 ቀን 2010 ዓ.ም. 

ዜናዎች
* የህወሃት መራሹ ቡድን ዘርፈ ጦር ዓላማ ጎንደር ላይ ተሸነፈ።
* በምስራቅ ኦሮሚያ የተፈናቃዮች ቁጥር ከ50 ሺ በላይ መድረሱ ታወቀ።
* በሀረር ተቃውሞ ያሰሙ ተፈናቃይ ነዋሪዎች ግድያ ተፈጸመባቸው።
የሰባአዊ መብቶች፣ በአርበኛ ታጋይ ገብርዬ ተፈራ
የሚሉትን ዜናዎችና ሙሉ ፕሮግራሞቻችንን በ http://www.patriotg7.org/ ላይ መከታተል የምትችሉ መሆኑን በአክብሮት እንገልፃለን፡፡

Monday, September 18, 2017

ESAT DC Daily News Mon 18 Sept 2017

Ethiopia will imperil without ability of people exercise civil, political rights: UN High CommissionerESAT News (September 18, 2017)

The UN High Commissioner for Human Rights said today that unless there is opening up of the political space in Ethiopia, the country is doomed to imperil.
Zeid Ra’ad Al Hussein was speaking in Washington, DC to members of the press and the human rights community, where he recalled that his team of human rights experts had been denied access by the Ethiopian regime following the deadly protests in 2015/2016 in which hundreds of protesters were shot and killed by the regime’s security forces.
The High commissioner hoped he and his experts would be given access when he visits the country again in January 2018.
He warned that unless the country opens up the political space and allow people to openly exercise their rights, the country risks a serious crises.
“Unless there was an opening of the system and the ability for people to exercise civil and political rights more openly, the country was imperilled,” Zeid Ra’ad Al Hussein said.
Al Hussein said he would form “a more conclusive opinion and picture” about the country after his trip in January.
The Ethiopian regime had refused demands by the High Commissioner and other rights watchdogs for an independent investigation into the killings of hundreds of anti government protesters in 2015 and 2016.

አርበኞች ግንቦት7 ንቅናቄውን ለሚቀጥሉት 3 ዓመታት የሚመሩትን መሪዎችን ይፋ አደረገ (ኢሳት ዜና መስከረም 08 ቀን 2009 ዓም)


ንቅናቄው በኤርትራ ሲያደርግ የነበረውን ጉባኤ ሲያጠናቅቅ ድርጅቱን ለሚቀጥሉት 3 ዓመታት የሚመሩትን መሪዎች በ4 ዘርፎች ከፋፍሎ ይፋ አድርጓል። እነዚህ ተመራጮች የስራ አስፈጻሚዎች ይሆናሉ።
ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ በሊቀመንበርነት በሚመሩት በዚህ የሃላፊነት ተዋረድ፣ ኮማንደር አሰፋ ማሩ የህዝባዊ ተጋትሮ ዘርፍን በአዛዥነት፣ አርበኛ ታጋይ ገበየሁ አባጎራውና አርበኛ ታጋይ ታደለ ወንድም በምክትል አዛዥነት ይመሩታል። በፖለቲካው ዘርፍ ደግሞ አርበኛ ታጋይ ኤፍሬም ማዴቦ በዘርፍ ሃላፊነት፣ አርበኛ ታጋይ ንአምን ዘለቀና አርበኛ ታጋይ አበበ ቦጋለ በምክትል ዘርፍ ሃላፊነት ይመራሉ። የህዝባዊ እምቢተኝነቱን ዘርፍ ዶ/ር ታደሰ ብሩ የሚመሩት ሲሆን፣ አርበኛ ታጋይ ቸኮል ጌታሁንና አርበኛ ታጋይ አብርሃም ልጃለም በምክትል ሃላፊነት ያገለግላሉ። የንቅናቄውን ጽ/ቤት ደግሞ አርበኛ ታጋይ መኳንንት አበጀ በሃላፊነት እንዲሁም አርበኛ ጃንከበድ ዘሪሁን እና አርበኛ ታጋይ መላኩ ተሾመ በምክትል ሃላፊነት እንደሚመሩት ንቅናቄው ገልጿል።

የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ ሬዲዮ

መስከረም 07 ቀን 2010 ዓ.ም.
ዜናዎች
* በሺዎች የሚቆጠሩ የኦሮሞ ተወላጆች ከሶማሌ ክልል መውጣታቸውን እንደቀጠሉ መሆኑ ታወቀ።
* በኦሮሚያና ደቡብ ክልል የተነሳው ግጭት ተባብሶ ቀጥሏል።
* በቆሼ ዳግም የቆሻሻ መደርመስ አደጋ ደረሰ።
ሳምታዊ የማህበራዊ መገናኛ ዳሰሳ፣ የአርበኞች ግንቦት 7፣ ለአንድነትና ለዴሞክራሲ ንቅናቄ፣ ባለፈው ሳምንት ውስጥ ባካሄደው የመጀመሪያ አጠቃላይ መደበኛ ጉባኤ ላይ ያተኮረ....

የሚሉትን ዜናዎችና ሙሉ ፕሮግራሞቻችንን በ http://www.patriotg7.org/ ላይ መከታተል የምትችሉ መሆኑን በአክብሮት እንገልፃለን፡፡

Sunday, September 17, 2017

Patriotic Ginbot 7 Adera Band New Afaan Oromo Song Hinkaature June 2017


አለም አቀፉ ተነባቢ ጋዜጣ Washington Post በፊት ለፊት ገፁ ላይ ስለ ንጉሱ ሰፊ ሽፋን ይዞ ወጥቷል። ፡


"…መላው አለም ቴዲ አፍሮን ይወደዋል! ከሀገሩ መንግስት በስተቀር" ~ @ዋሽንግተን ፖስት
(ሊንክ ለማይከፍትላችሁ ሰዎች እነሆ ሙሉውን እንደወረደ)
The world loves Ethiopian pop star Teddy Afro. His own government doesn’t.
By Paul Schemm
September 17, 2017 at 6:00 AM
Ethiopian pop star Teddy Afro at his home in Addis Ababa. (Mulugeta Ayene/Associated Press)
ADDIS ABABA, Ethiopia — Monday marked the first day of the new Ethiopian year, but it hasn't been much of a holiday for Teddy Afro, the country's biggest pop star.Image may contain: 1 person, smiling, sitting and indoor
First, the government informed him that his New Year's concert was canceled. Then, on Sept. 3, police broke up the launch party for his successful new album, "Ethiopia," in the middle of the sound check at the Hilton Hotel, claiming Teddy hadn't received permission to hold the event.
"Asking for a permission to organize an album launch is like asking a permit for a wedding or birthday party," Teddy wrote on his Facebook page. "This is unprecedented and has never been done before because it is unconstitutional."
But government disapproval certainly isn't anything new for Teddy: This year was his third straight aborted New Year's concert. And even as "Ethiopia," which briefly hit No. 1 on Billboard's world music chart, could be purchased or heard on virtually every street corner in the capital of Addis Ababa after its May release, Teddy's songs were nowhere to be found on state radio and TV. An interview with a public TV network was even canceled at the last minute, prompting the resignation of the journalist involved.
At first glance, there seems to be nothing controversial about Teddy Afro, born Tewodros Kassahun, and his traditionally influenced pop songs about love, unity and the glory of Ethiopia. His tunes have earned him a rapturous audience both at home and among the vast Ethiopian diaspora.
If anything, Teddy is quite the patriot. He's just the wrong kind of patriot.
Teddy's music has increasingly focused on extended history lessons glorifying Haile Selassie, the last emperor of Ethiopia, who was overthrown by a communist coup in 1974, as well as the great kings of the 19th century. The title track of his 2012 album, "Tikur Sew," for example, celebrated Emperor Menelik II and his defeat of Italian troops invading Ethiopia in 1896 — complete with a music video that was practically a war movie.
But those rulers came from the Amhara people, the ethnic group that has historically dominated the country and, according to other Ethiopian peoples, brutally repressed its rivals. "Wherever he faced fierce resistance, Menelik responded with the most barbaric and horrific forms of violence," read a statement by activists from the Oromo people in 2013, who led a boycott campaign of the Heineken-owned brewery Bedele after it sponsored Teddy's concerts.

ኢትዮጵያውያን በዘር ፍጅትና በእርስ በእርስ ጦርነት ከመተላለቃችን በፊት ሕወሐት/ኢሕአዴግ በአስቸኳይ ከስልጣን ይውረድ!!! (ከሰማያዊ ብሔራዊ ሸንጎ የተሰጠ መግለጫ)


ሕወሐት/ኢሕአዴግ ኢትዮጵያን ከፋፍሎና አዳክሞ ለመግዛት እና ዘላለማዊ ሰላሟን ለማናጋት ቅኝ ገዥዎች በተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የዘሩትን የጥላቻ መርዝ እንዳለ በመውረስና የአገዛዙ "ህጋዊነት ማላበሻ" ጨቋኝና ከፋፋይ ህገ መንግስት በማፅደቅ የኢትዮጵያውያንን የጋራ እሴቶች በማጥፋት ልዩነትን እያራገበ ኢትዮጵያን የመበታተን ሂደቱን ህጋዊነት አላብሶ የማፍረስ ተግባሩን ማከናወን ጀምሯል፡፡

በሕወሐት/ኢሕአዴግ ህገ መንግስት የስልጣን ባለቤቶች "ብሔር ብሔረሰብ" የሚባሉት ናቸው፡፡ ኢትዮጵያዊ ዜጋ ስልጣን የለውም፡፡ የፌደራል መንግስቱ አባላትም እነዚህ የብሔረሰብ/ጎሳ/ መንግስታት ናቸው፡፡ እነዚህ የጎሳ መንግስታትም እራሳቸውን ያለገደብ የማስተዳደርና ካልፈለጉም የፌደራል መንግስት አባልነታቸውን የመተውና የመገንጠል መብት ተሰጥቷቸዋል፡፡ ይህ የህገ መንግስት አስተሳሰብ የሚመነጨው ኢትዮጵያ የብሔረሰቦቸ እስር ቤት እንደነበረችና በሕወሐት/ኢሕአዴግ ህገ መንግስት ብሔረሰቦች ከእስር እንደተፈቱ በማመን ነው፡፡ በሕወሐት/ኢሕአዴግ አስተሳሰብ ቅኝት መሰረት ኢትዮጵያ የምትባለው ሉዓላዊት ሀገር እንደገና ተሰርታ "ብሔር ብሔረሰቦች" ተስማምተው የፈጠሯትና ሲፈልጉ የሚያፈርሷት የጎሳ ስብስብ ሆናለች፡፡
ይህ ከፋፍሎና አዳክሞ የመግዛት ዘይቤ በብዙ ኢትዮጵያውያን ላይ ተዘርዝሮ የማያልቅ ግፍና በደል እንዲፈፀም የህግ ሽፋን ሰጥቷል፡፡ በዚህም መሰረት
1.ከኦሮምያ ብሔራዊ መንግስት ሀገራችሁ አይደለም በሚል አማራዎች ከነነፍሳቸው በገደል ተጥለዋል፣በአሰቃቂ ሁኔታ ተገድለዋል፡፡ እንዲሁም ከደቡብ "ብሔር ብሔረሰብ" መንግስትና ቤንሻንጉል ጉምዝ መንግስት ሀብት ንብረታቸው ተቀምተው ሀገራቸውን ለቀው ወደ "አማራ ሀገር" እንዲሄዱ ተደርገዋል፡፡

Tensae Radio Sept 16 2017

Saturday, September 16, 2017

በወቅቱ የአገራችን ሁኔታ ላይ የአርበኞች ግንቦት 7 መግለጫ Patriot Ginbot7

September 16, 2017
አገራችን ኢትዮጵያ የምትገኝበት ወቅታዊ ሁኔታ እጅግ በጣም አሳሳቢ ነው። ህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) በኢትዮጵያዊያን ላይ በተለያዩ ግንባሮች ጦርነት ከፍቷል።
በሰሜን ጎንደር ጭልጋ፣ መተማና ሽንፋ አካባቢዎች ከፍተኛ ቁጥር ያለው ወታደር ሰፍሮ ሕዝብን ለመፍጀት ትዕዛዝ እየተጠባበቀ ነው። የአማራና የቅማንት ተወላጆችን ለማጋጨት ሲሸረብ የነበረው ዱለታ የመጨረሻ ደረሻ ላይ ደርሷል። የህወሓት አገልጋይ መሆኑ በተደጋጋሚ ባረጋገጠው የምርጫ ቦርድ አስፈፃሚነት ይካሄዳል የሚባለው ሕዝበ ውሳኔ ግጭትን ከማስፋት በስተቀር የሚኖረው ጠቀሜታ የለም። ሕዝበ ውሳኔው በራሱ አስፈላጊ አልነበረም፤ ይደርግ ከተባለም ምርጫው ሊያስፈጽም የሚችል ተዓማኒን ተቋም የለም። የሕዝበ ውሳኔው ውጤት ከምዝገባው በፊት መገመት የሚቻል ቢሆንም ድምፆች ተገልብጠው የውሸት ውጤቶች ይፋ እንደሚሆኑ ከወዲሁ መናገር ይቻላል። ብሔራዊ የምርጫ ቦርድ ከተቋቋመ ጀምሮ አንዴም ተዓማኒነት ያለው ምርጫ አስፈጽሞ የማያውቅ በመሆኑ አሁን የተለየ ነገር ይፈጽማል ብሎ ተስፋ ማድረግ አይቻልም። የአማራ ክልልና የትግራይ ክልል ተፈራረሙ የሚባለው የድንበር ማካለል ጉዳይም ሌላው ተቀጣጣይ እሳት ነው። ይህ ስምምነት የብአዴን አመራሮች የህወሓት አገልጋይነታቸውን መሬት በይፋ በመስጠት ያረጋገጡበት ሰነድ ሆኖ በሕዝብ ልብ ተመዝግቧል። ለወልቃይትና ቅማንት ጥያቄዎች ፈጽሞ የተለያዩ ምላሾችን መስጠት በራሱ ጠብ ጫሪነት ነው። ከዚህም በተጨማሪ ሰሜን ጎንደርን በሶስት ዞኖች የመሸንሸን እቅድ አለ። ህወሓት አማራን በአጠቃላይ፤ በተለይ ደግሞ ጎንደርን ለማዳከም ዘርፈ ብዙ ፕሮጀክቶችን ነድፎ እየተንቀሳቀሰ ነው።
በሶማሊ ክልል ያለው ሁኔታ እጅግ አሳሳቢ ነው። በጅጅጋ ከተማ እየተፈፀመ ያለ

የጥላቻ ፖለቲካ ውጤቱ የከፋ መሆኑን ለማገናዘብ ትንሽ የታሪክ ገጾችን ማገላበጥ በቂ ነው ( ጋዜጠኛ አበበ ገላው)


ሂትለር በአለማችን ላይ ተወዳዳሪ የሌለውን እልቂት የጫረው ጥላቻን በመስበክ ነበር። እኛ ታላቅ ዘር ነን፣ አይሁዳይውያን እና ሌሎች “ተውሳኮች” (vermins) ናቸው የሚለው ስብከት ተራውን ጀርመናዊ ዜጋ ብቻ ሳይሆን ምሁራን የነበሩ አዋቂዎችን ጭምር አስክሮና አነሁልሎ የግፍና እልቂት ተዋንያን እንዲሆኑ አድርጓቸው ነበር። የዘር ፖለቲካ ያለጥላቻና መከፋፈል አይሰራም። Bilderesultat for ጋዜጠኛ አበበ ገላው
ወያኔም ከምስረታው ጀምሮ ጥላቻን እየሰበከ አገሪቷን ለከንቱ አላማ በጦርነት እሳት ለበብልቦ የድሃ ገበሬ ልጅ በከንቱ አለቀ። ደርግ ወድቆ የተመኙት የስልጣን ወንበር ላይ ሲቆናጠጡ ባሰባቸው። ኢትዮጵያን በዘር ከፋፍለው ለእያንዳንዱ ብሄረሰብ ነጻ አውጭ ግንባር በማቋቋም በተለይ በአማራ ህዝብ ላይ አስከፊ የዘር ጥላቻ፣ የስነልቦና ጦርነት በመክፈት ማንንም በድሎ የማያቅ ምስኪን የአማራ ገበሬ ከየአካባቢው እንዲፈናቀል፣ እንዲገደልና በፍርሃት ተሸማቆ እንዲኖር አደረጉት። በበርካታ ሺዎች የሚቆጠሩ የአማራ ብሄር ተወላጆች በህወሃት ቆስቋሽነት ሲፈናቀሉና ሲገደሉ መለስ ዜናዊ በእብሪትና በጥላቻ ተውጥሮ የግፉ ሰለባዎች ዛፍ ስለመነጠሩ ነው የተፈናቀሉት ሲል በአደባባይ ተሳለቀባቸው። ድግነቱ የሚስኪኖችን እንባ የሚያብስ አምላክ ፍርዱን አላዛባም! 
በተለያዩ የአገሪቷ ክፍሎችም በሰላም የኖሩ ህዝቦች እንዲናቆሩ፣ ወድ ግጭትና መፋጠጥ እንዲያመሩ መንገዱን ሁሉ ጠረጉ። ይህ ሁሉ ሸር የከፋፍለህ ግዛው ፖሊሳያቸው እንዲሳካ የታለመ አሳፋሪና ሰብአዊነት የጎደለው እኩይ ተግባር ሲሆን ሌላውን እያናቆሩ እነርሱ አገሪቷን በዘረፋ እርቃኗን አስቀሯት። ለእነርሱ እድገት ማለት ሌላውን ወደኪሳራ እየገፉ፣ መሬት እየዘረፉ፣ ምስኪን እያፈናቀሉ አድሏዊ ግንባታና የአሻጥር ቢዝነስ መስራት ነው። የወያኔ ስኬት ባጭሩ ይሄው ነው። 

እፍታ ~ ጋዜጠኛ መሳይ መኮንን እና ሲሳይ አጌና በወቅታዊ ጉድያ ላይ ያደረጉት ውይይት

ከግጭቱ ማን ምን ያተርፋል? Wazema BL Special 091517

Friday, September 15, 2017

በደዋሌ እና በሽልሌ ዞኖች ይኖሩ የነበሩ የኦሮሞ ተወላጆች በልዩ ሐይል ፖሊሶች እየተፈናቀሉ ወደ ድሬዳዋ እየገቡ መሆኑ ተነገረ። ትንሳኤ ራዲዮ


ዛሬ መስከረም 5 ቀን ከማለዳ ጀምሮ የሱማሌ ክልልን ከሚያዋስኑ ሀገሮች መሀከል ከ 2 መቶ በላይ የሚገመቱ የኦሮሞ ተወላጆች ንብረት እና ገንዘባቸዉን ሳይዙ ለአመታት ከነሩበት መንደር ተሰደዉ ወደ ድሬዳዋ በመመግባት ላይ መሆናቸዉን ካካባቢዉ የደረሰን መረጃ አመለከተ፡፤የድሬዳዋ አስተዳደር በደዋሌ የቀሩትን የኦሮሞ ተወላጆች ለማምጣት ሰባት አዉቶቡሶች መላኩ ሲታወቅ ቀደም ብለዉ የገቡት ስደተኞች እስከ እኩለ ቀን ድረስ ምንም አይነት እርዳታ ሳይደረግላቸዉ ከቆዩ በሗላ፣ ከሰአት በሗላ ወደ ጫት መሀበር ግቢ እንደተወሰዱ እና ከሰዎች ጋር እንዳይገኛኙ እንደተደረጉም ያይን እማኞች ተናግረዋል፡፤ክልሉን ለቀዉ ከወጡት ግለሰቦች መሀልም የኦሮሞ ተወላጅ ያልሆኑ እና ድርጊቱን የተቃወሙ የሌላ ብሔር ተወላጆችም እንደሚገኙበት ታዉቋል። Image may contain: 2 people, people standing and outdoor
ስደተኞቹ ሰሞኑን የሱማሌ ልዩ ሀይል በሌሎች ክልሎች በሚኖሩ የኦሮሞ ተወላጆች ላይ እያደረጉት ካለዉን ኢሰብአዊ የማፈናቀል ድርጊት የተነሳ ስጋት ዉስጥ ገብተዉ እንደነበር ቢናገሩም፣ ምንም ሳይዘጋጁ እና ለመንገድ የሚሆናችዉ ነገር ሳይዙ በድንገት ከያሉበት እንደወንጀለኛ እየለቀሙ እንባረራለን ብለዉ አለመገመታቸዉን ተናግረዋል።አንድ ተፈናቃይ ከጎረቤቱ የቀብር ስነስርአት ላይ ተይዞ መመረጣቱንም በሀዘን ሲናገርም ተደምጧል።

Yared Negu - Yagute | ያጉቴ - New Ethiopian Music 2017 (Official Video)

በምእራብ ጉጂ ዞን በደቡብ ኮንሶ አዋሳኝ ድንበር ላይ ያካባቢዉ አርሶ አደር ከልዩ ሐይል ፖሊሶች ጋር ከፍተኛ ዉጊያ ላይ መሆኑን ከስፍራዉ የደረሰን ዜና አመለከተ። ትንሳኤ ራዲዮ

አራት ሰዎች መሞታቸዉ እና ሰባት መቁሰላቸዉም ታዉቋል፡፤
ያይን እማኞች እንደሚሉት ትላንት መስከረም 4 ማምሻዉ ላይ በጀመረዉ ዉጊያ ሌሊቱን የከባድ መሳሪያ ድምፅ የታከለበት ከፍተኛ የተኩስ ድምፅ ሲሰማ ማደሩን እና ከነጋ በሗልም ድንበር ላይ በምትገነዉ አሀረማርያም ወይንም ቡሌ ሆራ ከተማ ዉስጥ በመዝለቅ በነዋሪዎች ላይ ታጣቂዎች ሲተኩሱ እንደነበርም ተናግረዋል፡፤አክለዉም ትላንት ለሊት 4 ሰዎች ካርሶአደሮች መሞታቸዉን እና 7 ሰዎች መቁሰላቸዉን፣ የቡሌ ሆራ ሆስፒታልም በቁስለኛች ተጨናንቆ እንደሚገኝ፤ግማሹ ቁስለኛም ወደ ዲላ ሆስፒታል እየተጫነ መሆኑን ፣እንዲሁም ከገጠር ቀበሌዎችም ዛሬ ረፋዱ ላይ ቁስለኞች ወደ ሁስቲታሎች እየገቡ መሆናቸዉንም ጠቅሰዋል።Image may contain: one or more people and outdoor
ታርጋ ቁጥር 0241 እና 0252 የሆኑ የኦሮሚያ ፖሊስ መከላከያ ፒካፕ ተሽከርካሪዎች፤ ለልዩ ሐይል ታጣቂዎች መሳሪያን እና ስንቅን ጨምሮ የሚያስገልጋቸዉን ግብአቶች እየተመላለሱ ሲያቀብሉ መታየታቸዉንም ባካባቢዉ የነበሩ ያይን እማኞች ሲናገሩ፤በሌላ በኩል የአገዛዙ አባላት ጥቃቱን እየፈፀሙት ያሉት በድንበር ግጭት ሰበብ የኮንሶ ተወላጆች እንደሆኑ ለማስመሰል ሙከራዎች እያደረጉ እንዳለ ጠቅሰዋል። ሆኖን ያካባቢዉ አርሶ አደር እና ነዋሪ ጥቃቱን እየፈፀመ ላለዉ እና የህዉሀት አገዛዝ ጉዳይ አስፈፃሚ ነዉ ሲሉ ለሚቀሱት ልዩ ሀይል በመተባበር ምላሽ እየጡ መሆናቸዉን ገልፀዋል።

ESAT Daily News Amsterdam September 15,2017

ESAT TIGRIGNA NEWS SEPTEMBER 15,2017

[PG7] ከአርበኞች ግንቦት 7፣ ለአንድነትና ለዴሞክራሲ ንቅናቄ፣ አንደኛ መደበኛ ጉባኤ ለኢትዮጵያ የመከላከያና የፖሊስ ሰራዊት ዓባላት በሙሉ፣

የወያኔ ዘረኛና አምባገነን ሥርዓት፤ እድሜውን የሚያራዝመው፣ መብቱንና ነጻነቱን ለማስከበር የሚታገለው ወገናችሁ ላይ በየጊዜውና በየቦታው አሰቃቂ ርምጃ እንድትወስዱ በማድረግ ሲሆን፣ በሌላው ጎኑ ይህ ሥርዓት ከአናቱ እየፈረሰ መሆኑ ደግሞ ከእናንተ የተሰወረ እንዳልሆነ ግልጽ ነው።
በቅርብ የምታውቋቸው አለቆቻችሁ ከሲቪል አቻዎቻቸው ባልተናነሰ ሁኔታ በከፍተኛ ዘረፋ በተዘፈቁበት አጸያፊ ድርጊት ምን ያህል ሀብት እንዳካበቱ የአደባባይ ሚስጥር መሆኑን ታውቃላችሁ።

ስለዚህ የእናንተ ከዚህ ከበሰበሰና ሊወድቅ እያዘመመ ካለ ሥርዓት ጋር መቆም፤ በሀገራችሁ እና በወገናችሁ ላይ ከሚያስከትለው ሰቆቃ በሻገር፤ እናንተም የስርዓቱ አሰቃቂ ርምጃዎች አስፈጻሚ እና ቀጥተኛ ተሳታፊ መሆናችሁ የተለየ ሀላፊነትን አሸክሟችኋል። በመሆኑም የወያኔን ያበቃለት የአገዛዝ ሥርዓት ዛሬውኑ ትታችሁ እና በሚቻላችሁ ሁሉ በሕዝብ ላይ የምታደርሱበትን ሰቆቃ አቁማችሁ፣ ከወገናችሁ ጎን እንድትቆሙና በምትችሉት አጋጣሚ ሁሉ ንቅናቄያችንን እያካሄደ ያለውን ትግል እንድታግዙ፤ ከተቻለም ንቅናቄያችንን እድትቀላቀሉ በራችን ክፍት መሆኑን ጉባኤያችን ያረጋግጥላችኋል።

Thursday, September 14, 2017

Bewketu Sewmehon - Gojam | ጎጃም - New Ethiopian Music 2017 (Official Video)

የአሜሪካ ብሔራዊ የደህንነት ኤጀንሲ የኢትዮጵያው አገዛዝ ዜጎቹን እንዲሰልል የቴክኖሎጂ እገዛና ስልጠና እየሰጠ መሆኑን ኢንተርሴፕት የተባለ ተቋም አጋለጠ። (ኢሳት ዜና–መስከረም 4/2010)

ብሔራዊ የደህንነት ኤጀንሲው በኢትዮጵያ የስለላ መረብ እንዲዘረጋ ትልቅ እገዛ ማድረጉን መረጃዎቹን ያሰባሰበው ይሄው ተቋም ገልጿል። የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በየአመቱ የሀገራትን ሰብአዊ መብት አያያዝ በማስመልከት በሚያወጣው መግለጫ ኢትዮጵያ ዜጎቿን መሰለሏንና ማፈኗን ቢያወግዝም የዚሁ ድርጊት ተባባሪ መሆኑ ግን ትክክል አለመሆኑን ተቋሙ ተችቷል።No automatic alt text available. አሜሪካ የኢትዮጵያ ዜጎች እንዲሰለሉና እንዲታፈኑ በሚያስችለው የደህንነት ቴክኖሎጂ መረብ ዝርጋታ እጇ አለበት መባሉ ጉዳዩን ውስጡን ለቄስ አስብሎታል። በአንድ በኩል ኢትዮጵያ የሰብአዊ መብት ረገጣ ትፈጽማለች በማለት የምታወግዘው ዩናይትድ ስቴትስ ኦፍ አሜሪካ በሌላ በኩል የጉዳዩ ተባባሪ ሆና መገኘቷ ብዙዎችን አስገርሟል። ኢንተርሴፕት የተባለው ተቋም ሚስጥራዊ ሰንዶችን በመመርመር ይፋ እንዳደርገው የአሜሪካ ብሔራዊ የደህንነት መስሪያ ቤት ኢትዮጵያ የዜጎቿን የስልክ ግንኙነትና ንግግሮችን የሚጠልፍ የቴክኖሎጂ መረብ እንድትዘረጋ ከፍተኛ የቴክኖሎጂና የስልጠና ድጋፍ አድርጓል። በአንድ በኩል በልማትና በጤና እንዲሁም በሰብአዊ ጉዳይ ላይ ብቻ እርዳታ እሰጣለሁ እያለች የምትፎክረው አሜሪካ በሌላ ሁኔታ የኢትዮጵያውያን መብት እንዲጣስና እንዲታፈን በሚያደርግ ወንጀል ተባባሪ መሆኗ ትልቅ ችግር መሆኑን ኢንተርሴፕት ዘርዝሯል። እንደ ተቋሙ ገለጻ አሜሪካ ለኢትዮጵያ የስለላ መረብ መረጃ የቴክኖሎጂና የስልጠና አገልግሎት ስትሰጥ የቆየችው ሽብርተኝነትን ለመከላከል በሚል ሰበብ ነው። ይህም ሆኖ ግን የኢትዮጵያ አገዛዝ ይህን ቴክኖሎጂ ለሰብአዊ መብት ረገጣና ለአፈና እየተጠቀመበት መሆኑን አሜሪካ እያወቀች ይህን ማድረጓ አግባብነት የለውም ብሏል። ኢትዮጵያ የተቃዋሚ መሪዎችንና ጋዜጠኞችን በማሳደድና በማሰር እንዲሁም ዜጎችን በመግደል ወንጀል እየፈጸመችበት መሆኑንም ኢንተርሰፕት የተባለው ተቋም ገልጿል። አሜሪካ ለኢትዮጵያ መንግስት የስለላ መረብ የሰጠችው የቴክኖሎጂ መረብ የአንበሳው ኩራት ወይም ላየንስ ፕራይድ የተሰኘ ነው። ይህም እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር ከ2002 በትንሽ የሰው ሃይል ጀምሮ በ2005 ወደ ከፍተኛ ደረጃ ያደገ ነው ተብሏል። በዚህ ፕሮጀክት 8 አሜሪካውያንና 103 ኢትዮጵያውያን ተሳትፈዋል ተብሏል። ፕሮጀክቶቹም በአዲስ አበባ፣በድሬደዋና በጎንደር ከተሞች የተዘረጉ መሆናቸው ነው የተገለጸው። በእነዚህ ፕሮጀክቶችም 7 ሺ 700 ሰንዶችና 900 ሪፖርቶች ከስለላ ስራው በኋላ የተዘጋጁ መሆናቸውን ኢንተርሴፕት አጋልጧል።

Teddy Afro - Mar eske Twauf (ማር እስከ ጧፍ) | New Official Video - 2010/2017

(Surafel Real Habesha)
⇩⇩⇩
በአምለሰት ሙጬ ተዘጋጅቶ በማያ ፊልም ፕሮዳክሽን
የቀረበ የፍቅር እስከ መቃብር አጭር ታሪክ!!! (የሙዚቃ
ቪዲዮ ከምል ይልቅ አጭር ፊልም ብለው ስራውን
በደምብ ይገልፃል)
☞ ገና ቪዲዮ ሲጀምር "ማር እስከ ጧፍ" ተብሎ
የተፃፈበት መንገድ በራሱ የሙዚቃውን ሀሳብ
ይገልፀዋል። ማር አንድም ይጥማል አንድም ጧፍ ሆኖ
ይነዳል። ይነዳል የሚለው ቃል በራሱ ኹለት ትርጉሞች
ይኖሩታል። አንድም መንደድ/መቃጠል ሲሆን ሌላው
ደግሞ መናደድ ነው። በግጥሙ ላይም እንደተመለከትነው
☞ ማር እስከ ጧፍ ሁኖ ዓለም ቢነዳቸው ☜ ይላል
ሰብለወንጌል ዓለም በቃኝ ብላ መመነኗን እንዲናገር!!!
☞ ቪዲዮ ሲቀጥል አስቀድሞ የተዜመ የግዕዝ ቃል አለ።
"ዝ ጠላ ከመ ወይን ጣዕሙ
እስኩ ድገሙ ድገሙ እስኩ ድገሙ"
ይህ ጠላ እንደ ወይን ይጥማል። ድገሙ እንደማለት ነው።
(የግዕዝ ዕውቀት የለኝም) ☞ ሰብለወንጌል የንጉሥ ዘር
ያለበት ቤተሰብ ውስጥ ነበር የምትኖረው። ስለዚህም
በቤታቸው ጥዑም የሆነ ጠላ እንደ ወይን የሆነ ተትረፍርፎ
እንደሚገኝ ያወሳል። ነገሩ ጠላ ተባለ እንጂ ውስጣዊ
ትርጉሙ ከማር የተሰራ የሚጣፍጥ ጠጅ እንደማለት ነው።
ይህንንም በቪዲዮ ውስጥ ጠጅ ሲጠጡ አስመልክቶናል።
ስለዚህም ሰብለወንጌል ሁሉ ነገር የተትረፈረፈበት የንጉሥ
ቤት ውስጥ እንደምትኖር ያመሰጥራል።
☞ አሁንም ይህ ድንቅ ቪዲዮ ሲቀጥል ሎሬቱ የክቡር
ዶክተር ሐዲስ አለማየሁን ፍቅር እስከ መቃብር እያነበበ
እና የከያኒ ወጋየሁ ንጋቱን ትረካ እየሰማ ያሳየናል።
ትረካውም እንዲህ ይላል " ... የተከደኑ አይኖቹን ገለጥ
አድርጎ ከፊቱ የቆሙትን መነኩሴ አየና "ሰብለ" አለ ጣር
በሚጎትተው ድምፅ ... " ይላል። በዛብህ ሰብልዬን ፍለጋ
ከሀገር ሀገር ሲዞር በአጋጣሚ ሽፎታዎች በደበደቡት ጊዜ
ሰብለወንጌል መንኩሳ ኖሯል ለካ!!! ሰብልዬም በዛ ጊዜ
በዛብህ መሆኑን አላወቀችም ነበር። "ሰብለ" ሲላት ጊዜ
ግን በዛብህ እንደሆነ አወቀች። ልታድነውም ጣረች። ነገር
ግን በጣም ተደብድቦ ነበርና በዛብህ ሊተርፍ አልቻለም።
በዛብህ ከተቀበረበት መሬት አጠገብ ሰብልዬ ለራሷ
ጉድጓድ አስቆፍራ ነበር። (ስትሞት ከአጠገቡ እንድትቀበር
ዘንድ) ይህንን ታሪክ ሊያስቃኘን ወደደና ይህን ትረካ
አስገባው ሎሬቱ!!!
☞ ከዚህ ለጥቆ ሎሬቱ ማንበቡን ገታ አድርጎ ሃሳብ
ውስጥ ሲገባ ዋናው የሙዚቃ ቪዲዮ ይጀምራል
የ ማር እስከ ጧፍ ግጥምም ዋና ሀሳቡ ከላይ
እንደተገለፀው ☞ በዛብህ የሰብልዬን ምንኩስና
በተመለከተ ጊዜ ምን ይናገር ነበር? የሚለው ነው።
ይህንንም በቪዲዮ ውስጥ ባማረ ሁኔታ ተመልክተነዋል።
☞ የሙዚቃ ቪዲዮ ባማረ ሁኔታ (በጥሩ ሁኔታ ከተሰራ
ፊልም ጋር በሚመሳሰል መልኩ) እስከመጨረሻው
ይዘልቃል። በተለይም የሰብልዬ እና የፊትአውራሪ መሸሻ
ገፀባህርያት ትወና የሚደንቅ ነበር።
በዚህ ድንቅ ሥራ መሀል የተካተቱትን ኹለት ቦታዎች
ብቻ ጠቀስ ላድርግ
① ጉዱ ካሳ ሰብለወንጌል ከመነኮሰች በኋላ ከሷ ዘንድ
ሲሄድ እና
② ፊትአውራሪ መሸሻ ፈረስ እየጋለቡ ሳለ ፈረሱ ከገደል
ጥሏቸው ሲሞቱ (እዚህ ጋር እንኳን ሰው ፈረስም
ይተውናል የሚያስብል ነው) ፊትአውራሪ ሲሞቱ ሰብልዬ
ላይ የነበረው ሀዘን የአምለሰትን የትወና ብቃት
ይመሰክራል።
☞ ሙዚቃው ከተገባደደ በኋላ ሎሬቱ በድጋሚ የፍቅር
እስከ መቃብርን መፅሐፍ እያነበበ (የሚያነበው መፅሐፍ
ያረጀ ነው። የፍቅር እስከ መቃብርን ታላቅነት በእርጅናው
አሳይቶናል) የከያኒ ወጋየሁ ንጋቱ ትረካ ይንቆረቆራል።
(የመተረኪያው ራዲዮም በድሮ ጊዜ የነበረ መሆኑ
የትረካውን ዕድሜ ያሳያል) ①* " ... ጉዱ ካሳ እና ሰብለ
በተገናኙ በአስራ አምስተኛው ቀን ሰብለ የልብ በሽታዋ
ተነሳ እና እንደልማዷ ወደቀች። ነገር ግን ዳግም
አልተነሳችም!!! " ከዚህም በኋላ ሰብልዬ አስቀድማ
ባዘጋጀችው መቃብር ከበዛብህ አጠገብ ተቀብራ
# ፍቅር_እስከ_መቃብር ሆነ። ጉዱ ካሳም አብሮአቸው
ተቀበረ።
☞ በስተመጨረሻም ይህን ሥራ ለክቡር ዶክተር ሐዲስ
አለማየሁ እና ለከያኒ ወጋየሁ ንጋቱ አበርክቷል። እዚህም
ጋር ለፊተኞቹ የሚገባቸውን ክብር በሚገባቸው ሥራ
ሰጥቷል። ብዙ ሰዎችን ካመሰገነ በኋላ በልዩ ምስጋና ላይ
የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ በቅድሚያ አመስግኗል። ይህም
የሙዚቃው ቪዲዮ ሲሰራ ታሪክ ሳያዛባ በጥበብ እና
በጥንቃቄ እንደሰራው ያሳየናል።
# እናመሰግናለን_ቴዲያችን
ፍቅር ያሸንፋል!!
https://m.youtube.com/watch?feature=youtu.be&v=u2inQ1WeaFs

በጉጉት ሲጠቅ የነበረው «ታኦማጎሲስ»(የእግዚአብሔር ጠላቶች) የተሀድሶ መናፍቃንን የሚያጋልጠው የሀዋሳው ዘጋቢ ፊል...

ከውስጥ አርበኞች አስቸኳይ መርጃ ተልኳል ሺር በማድርግ ለወገናችን በፍጥነት መረጃውን እናድርስ!!!!


ከመቸውም በላይ የትግራይ ሹማምንት በጎንድር ህዝብ ላይ የደገሱትን ድግስ ለማስፈፅም ሊት ተቀን በመራወጥ ላይ መሆናችውንም አያይዞ ጠቅሰዋል ጎንደር አዞዞ የጦር ካምፕ ውስጥ የአማራ ተወላጅ የሆኑትም መከላከያእያነሱ በምትካቸው ከትግራይ የመጡ መከላከያዎች ተቀላቅለዋል፡ ጭልጋ ሠራባ ያለው የጦር ጋምፕም የአማራና የኦሮሞ መከላከያ ተነስተው ከትግራይ በመጡ ወታደሮች ተቀላቅለዋል፡ በአጠቃላይ ጎንድር ዙሪያ በትግራይ በመጡ ጭንብል ባጥለቁ ተጠቅልቃለች ይላል መረጃው።
አቶ አባይ ወልዱ የጦር መሳሪያዎችና ጥይቶችን ፈንጆችን፡ በአንቡላንስና በመንግስት ሽፍን መኪና እያጓጓዘ ነው። በወሎ በኩል በጋይንት አድርገው ገሚሶቹ እብደሚላኩ መረጃው ይጦቁማል ፡ ከመቀሌ በማይፅብሬ አድርገው አዳርቃይን ዛሬማን ሊማሊሞን አድርጎ ወደ ጎንደር ከዛም ጭልጋላይ ይራገፍና ማውራ ላይ ለህዝብ እያስታጠቁ መሆኑን ተደርሶበታል ሰራባ፡ትግክል ድንጋይ፡አንችው ሚካኤል፡ሮቢት፡ግንድ መጣያ፡እንዲብና፡ጫጮቁና፡ውናኒያ፡በነዚህ በተጠቀሱት ቦታዎች ሰዎችን በሚንሻ መልኩ እያስታጠቁ መሆኑና አይዟቹህ የትግራይ ህዝብ ከጎናቹህ ነን በማለት የተለያየ የመደለያ ሰነድ አዘጋጅተው በመስጠት ላይ ይገኛሉ።
በሊላ በኩል ካአዲስ አበባ በደብረፆንና በአባይ ፃሃየ የተለያየ የገንዘብ ድጋፍ ለማድርግ በሊሊት ጎንደር በካድሬዎች ለኮሚቲ በሚል የመደለያ ገንዘብ እያከፋፈሉ ነው።
በአጠቃላይ የጎንድርን ህዝብ የመከፋፈሉ ሲራ ለኢትዮጵያ ትልቅ ውድቀት ነው፡ የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ ለምህራኖች በሀገር ውስጥም በውጭም ለምትኖሩ ይህ ለእናተ የቤት ሥራነው ሀገራችን ከጥፋት እንታደግ ጥሪያችን ይድረስ።
ድል ለጭቁኑ ህዝባችን።
ሞት ለባንዳ ህወሀት ወያኔ ህርነት ትግራይ
ካ•መ አሞራው ምንአለ ባሻ - 14/98/201

"ኢትዮጵያዊ በመሆኔ ብቻ የጀመርኩትን የዶክትሪት ትምህርትን ተከልክዬ ወደ አገሬ ተባረርኩ" አሳዛኙ የኢትዮጵያዊው ...

ማሳሰቢያ Esat

ብዙ አሰቃቂ መረጃዎች እየደረሱን ነው። ብዙዎችን መረጃዎች ለህዝብ ደህንነት ሲባል አናወጣቸውም። ለማንኛውም ግን ግጭቱ በሶማሊ እና በኦሮሞ ህዝብ መካከል አለመሆኑን ሁሉም ወገን ሊገነዘበው ይገባል። በህዝብ እና በአገዛዙ መካከል ያለውን ግጭት የህዝብ ለህዝብ ግጭት አስመስሎ ለማቅረብ የሚደረገው ጥረት በጊዜ ካልቆመ አደጋው ለሁሉም ይተርፋል። ይህ ግጭት በአገዛዙና በህዝብ መካከል ብቻ መሆኑን በሶማሊ እና ኦሮምያ አካባቢዎች የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን መልዕክት እንድናስተላልፍላቸው በገለጹልን መሰረት መልዕክቱ እንዲተላለፍ አድርገናል።
14 - 09 - 2017

የአርበኞች ግንቦት 7፣ ለአንድነትና ለዴሞክራሲ ንቅናቄ፣ ባካሄደው የመጀመሪያው አጠቃላይ ጉባኤ ላይ ያተኮረ ልዩ ፕሮግራም ይዘናል... (የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ ሬዲዮ)



የሚሉትን ሙሉ ፕሮግራሞቻችንን በ http://www.patriotg7.org/ ላይ መከታተል የምትችሉ መሆኑን በአክብሮት እንገልፃለን፡፡Image may contain: one or more people and people sitting