Tuesday, May 31, 2016

ህዝቡ “ለቀብራችን ደርሳችሁዋል” በማለት ለኢህአዴግ “ምስጋናውን” አቀረበ ግንቦት ፳፫(ሃያ ሦስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና

- 25ኛ አመቱን በማክበር ላይ ያለው ኢህአዴግ ፣ ህዝቡን ለማወያየት በባህርዳር በጠራው ስብሰባ ላይ አባሎቹ “ ኢህአዴግ ለቀብራችን ደርሰህልናልና እና እናመሰግንሃለን” ሲሉ ተሳልቀውበታል።

አንድ  አስተያየት ሰጪ “ይህ ህዝብ ያለቀና የሞተ ህዝብ ነው፤  አሁን ነው እንዴ የምትመጡት? ፣ ለህዝቡ ቀብር መጥታችሁዋል ጥሩ ነው ያሉ ሲሆን መንግስት በዲሞክራሲ ረገድ አገኘሁት በማለት ያቀረበውን የድል ዜና ውድቅ አድርገውታል። በየበረንዳው ወድቀው ያሉ፣ መጠጊያ የሌላቸው ከማህበራዊ ህይወትና ከኢኮኖሚ የተገለሉ አባላት አሉን ሲሉ አስተያየት ሰጪው በምሬት ተናግረዋል ።
ተናጋሪው የቤት ችግር በተመለከተ የቀረበውን ሪፖርት ሲያጣጥሉም፣ “ ዋናው አውራ ጎዳና ላይ የተገነባው እኮ የካቢኔ ቤት ነው፣  የትኛውን የህብረተሰብ ክፍል አቅፎ ነው ተሰርቷል የምትሉት ግንባታ አሳፋሪ ነው ሲሉ አክለዋል።  አስተያየት ሰጪው የ ኢህአዴግ ባለስልጣናት ነገ መቃብር ውስጥ ገብተው ሙታኖችን እንደማይዘርፉ ዋስትና የለንም ሲሉ ያክላሉ ።

Monday, May 30, 2016

ጠላቶቻችን ወደ ውስጥ ሰርገው በመግባት ሊያዳክሙንና ሊያሽመደምዱን እየሞከሩ ነው ሲል ኢህአዴግ አስታወቀ ግንቦት ፳፪ (ሃያ ሁለት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-

 25ኛውን የግንቦት20 በአል በማክበር ላይ የሚገኘው ኢህአዴግ ለውይይት ባዘጋጀው ሰነዱ ላይ ግንባሩ ከፍተኛ አደጋ ውስጥ መውደቁን አትቷል። ባለፉት 25 አመታት ከፍተኛ ድል በኢኮኖሚ፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ መስኮች የተመዘገበ ቢሆንም፣ እነዚህን ድሎች የሚቀለብሱ እንዲሁም የአገሪቱን ህልውና አደጋ ውስጥ የሚጥሉ አዝማሚያዎች እየታዩ ነው ብሎአል።

ኪራይ ሰብሳቢዎችና የኒዮ ሊበራል ሃይሎች ከውጭ ሆነው ከሚያካሂዱት ጥቃ

ጠላቶቻችን ወደ ውስጥ ሰርገው በመግባት ሊያዳክሙንና ሊያሽመደምዱን እየሞከሩ ነው ሲል ኢህአዴግ አስታወቀ


ግንቦት ፳፪ (ሃያ ሁለት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- 25ኛውን የግንቦት20 በአል በማክበር ላይ የሚገኘው ኢህአዴግ ለውይይት ባዘጋጀው ሰነዱ ላይ ግንባሩ ከፍተኛ አደጋ ውስጥ መውደቁን አትቷል። ባለፉት 25 አመታት ከፍተኛ ድል በኢኮኖሚ፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ መስኮች የተመዘገበ ቢሆንም፣ እነዚህን ድሎች የሚቀለብሱ እንዲሁም የአገሪቱን ህልውና አደጋ ውስጥ የሚጥሉ አዝማሚያዎች እየታዩ ነው ብሎአል።
ኪራይ ሰብሳቢዎችና የኒዮ ሊበራል ሃይሎች ከውጭ ሆነው ከሚያካሂዱት ጥቃት በተጨማሪ ወደ ውስጣችን ሰርገው በመግባት መንግስታችንን ለማዳከምና ለማሽመድመድ እየሞከሩ ነው ያለው ኢህአዴግ፣ “ ‘ማንኛውንም የተቀናቃኝህ ምሽግ ለመያዝ ቀላሉ መንገድ ከውስጥ ነው” እንደሚባለው በውስጣችን የራሳቸውን ወኪሎች በመመልመል፣ በሙስና ሊማረኩ የሚችሉትን በመማረክ ድርጅታችን የተቀደሰ አገራዊ ተልእኮውን እንዳይፈፅም እስከማደናቀፍ ይደርሳሉ” ብሎአል።
ግንባሩ አያይዞም “ ድርጅታችንና በእርሱ የሚመራው ትግል በብዙ መስኮች ከባድ ፈተናዎችና አደጋዎች እየተጋረጡባቸው” በመሆኑ፣ 25ኛውን አመት በአል ጥልቀት ያለውና መሰረታዊ የራስ ምልከታ ለማድረግ መጠቀም አማራጭ የሌለው ሆኖ ተገኝቷል ብሎአል።
ኢህአዴግ ህዝቡ ትእግስቱ እየተሟጠጠ መምጣቱን እና መብቱን ለማስከበር መታገል መጀመሩንም በሰነዱ አሰፍሯል።

ዜና መረጃ — በረከት ስሞን አርበኞች ግንቦት 7 ያለዉ ዉስጣችን ነዉ ይላሉ!!

ወሎን ሰፈር ተሻግሮ ሩዋንዳ ሙልሙል ዳቦ አካባቢ ወደ ቦሌ በሚወስደዉ መንገድ በስተቀኝ ወደ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርስቲ ይገኛል ከዩኒቨርሲቲዉ በተጓዳኙ በስተግራ ካለዉ ነጭ ህንጻ ላይ በደረጃ ቀስ እያልን ወደ 5ተኛ ፎቅ አመራን፣ ከቢሮዉ በተያያዘ ቱሪዝም ኤጀንሲ ባጎራባች ሲኖር ከስሩ ደግሞ ሱፐር ማርኬት አለ በዋናነት ወደዛ የሄድንበት ምክንያት የበረከት ስሟን ቢሮ እዚያ እንደሚገኝ በደረሰን መረጃ መሰረት ነዉ።
ቢሮዉ እነደደረስን ጸሐፊዉን ለማግኘት ትንሽ ብንጠብቅም አግኝተን አናገርናት የበረከት ስሞን ቢሮ መሆኑን ካረጋገጥን በኍላ ትንሽ ጠብቁ ተብለን ተቀመጥን ከጥቂት ቆይታ ወዲህ በረከት በሁለት ሰዎች መካከል ሆኖ ከተፍ ሲል ተመለከትነዉ የመሰብሰቢያ፣ ቢሮ በመሰለዉ ቢሮ ዉስጥ በአይኑ ሁላችንንም ገርበብ አድርጎን በአንገቱ ሰላምታ ሰጥቶን ወደ ዉስጥ ዘለቀ!
እኛም እዚያዉ መጠበቅ ጀመርን ከጥቂት ቆይታዎች በኍላ እቃ እንደረሳንና በሌላ ቀን እንደምንመለስ ለጸሐፊዋ ነግረን ተመልሰን ወጣን።
መኪናችን ዉስጥ ገብተን ወደተቀመጥንበት ሆቴል ገሰገስን ክፍላችን ዉስጥ እንደገባን መቀረጸ ድምጻችንን በቢሮዉ ዉስት እንደምን ጥለነዉ እንደወጣን እየተወያየን ተዝናናን ክትትላችንንም በመጠኑ በተለያዩ አካሎቻችን በማከናወን መግቢያ መዉጫቸዉን አጠናን ከ3 ቀናት በኍላ የተቀረጸዉን ድምጽ በጥቂቱ ይህን ይዟል።
— አቶ በረከት... አርበኞች ግንቦት 7 በየሐገሩ በየቦታዉ የተደራጀ ሐይል አለዉ ከእንግዲህ አ/ግንቦት 7 ልግባ መንገድ ልቀቁልኝ ወይም አሳልፉኝ አይልም ከእንግዲህ አ/ግንቦት 7 ገፍትሮንም አይገባም አ/ግንቦት 7 ያለዉ ዉስጣችን ነዉ! ከባዱ ስራ የሚሆነዉም ይህዉ ነዉ! የሚጠረጠሩ ግለሰቦች በሙሉ የመኖሪያና የመስሪያ ቦታቸዉ ድረስ እየተዞረ የፎቶና የተለያዩ ተጨባጭ መረጃዎች ይያዝ! ያለበለዚያ ምን እንደምንሰራ አይገባንም።
— አቶ ሳህረ የሚባል የብሄራዊ መረጃ ተወካይ.... በትክክል ብለዋል አቶ በረከት አባሎቻችን መንግስታዊ ካልሆነ ድርጅት ነዉ የመጣነዉ እንዲሁም ከማህበራዊና ቱሪዝም ቢሮ ነዉ የመጣነዉ እያሉ ቤት ለቤት ሁሉ እየዞሩ ነዉ። ግን መረጃዎችን ለማግነት ይህ ብቻ በቂ ነዉ ብለን አናስብም።
በሌላኛዉ እለት እዚያዉ ቢሮ ተገኘንና አቶ በረከትን አነጋግረን ድምጸ መቅረጻችንን ካስቀመጥንበት አንስተን ወጣን እንግዲህ በአሁኑ ወቅት ወያኔ ይህዉ ነዉ።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!

Sunday, May 29, 2016

ሜ/ጄኔራል አበበ ተ/ሃይማኖት ለኢሕአፓ፣ መኢሶን፣ ኦነግ፣ ሲነግ ክሬዲት ሰጡ – “ተወልደ፣ ፃድቃን፣ ስዬና ተፈራ ዋልዋ ስለአሰብ ጥያቄ ያነሱ ነበር” አሉ

በሕወሓት ክፍፍል ወቅት ስልጣናቸውን እንዲያጡ የተደረጉት የቀድሞ የኢትዮጵያ አየር ኃይል አዛዥ ሜጀር ጄኔራል አበበ ተክለ ሃይማኖት ደርግን ለመጣል ለተደረገው ትግል ኢሕአፓ፣ መኢሶን፣ ኦነግ፣ ሲነግና ወዘተ አስተውጽኦ እንደነበራቸው ተናገሩ:: ጄነራሉ ከሪፖርተር ጋዜጣ ጋር ግንቦት 20ን በማስመልከት ባደረጉት ንግግር ስለአሰብ ወደብ ጉዳይም ተናግረዋል:abebe Tekelehianot:
“ድሮም ቢሆን የኤርትራን ነፃነት ተቀብለው የአሰብ ጉዳይ ላይ ጥያቄ የሚያነሱ ሰዎች ነበሩ። እንደነ አቶ ተወልደ ወልደ ማርያም፣ ሌተና ጄኔራል ፃድቃን ገብረ ትንሳኤ፣ አቶ ስየ አብርሃ፣ አቶ ተፈራ ዋልዋ፣ እኔም ጥያቄዎች የምናነሳበት ሁኔታ ነበር፡፡ በዝርዝር ባንወያይበትም። አሜሪካ ሄጄ ሁለተኛ ዲግሪዬን ስሠራ ግን በዚህ ላይ ጥናት አካሂጄ የባህር በር መብታችንን በሕጋዊ መንገድ ማስመለስ እንደምችል የሚያረጋግጥ ድምዳሜ ላይ ደረስኩ። ባለማወቅና በመታበይ (Ignorance and arrogance) ያጣነው መብት ነው፡፡ አሁንም ግን ሕጋዊ መሠረት አለን፡፡”
ያሉት ጀነራሉ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል::
አሁን እየተነሱ ባሉት የህዝብ እንስቅቃሴዎች ዙሪያ ከሪፖርተር:-
“ሕዝባዊ አመፅ እየታየ ያለው በተካሄደው ምርጫ ገዢው ፓርቲ መቶ በመቶ ማሸነፉን በገለጸበት ማግሥት ነው፡፡ ይህን ያህል የሕዝብ ተቃውሞ መነሳቱ በምርጫ ሒደቱ ላይ ጥያቄ አያስነሳም?” የሚል ጥያቄ የቀረበላቸው ሜጀር ጀነራል አበበ ” የመንግሥትና የፓርቲ መዋቅሮች መደባለቅ አንዱ ትልቅ ችግር ነው። ኢሕአዴግ የመንግሥት ሚድያ፣ የመንግሥት ቢሮ፣ ገንዘብና አሉ የሚባሉ እርከኖችን ለፓርቲ ሥራ ስለሚያውል የፉክክር ሜዳው ዴሞክራሲን የሚያስችል (democracy enabling) እንዳይሆን አድርጎታል። ቻርለስ ቲሊ የሚባል ታላቅ የፖለቲካ ሳይንቲስት አንድ ፓርቲ ከሰባ አምስት በመቶ በላይ የፓርላማ መቀመጫዎችን ለብቻው ከያዘ ገና ከወዲሁ ዴሞክራሲያዊና ፍትሓዊ ያልሆነ፣ በሕዝብ ተቀባይነት የሌለው ምርጫ ነው ማለት ይቻላል ይላል። ምክንያቱም አንድ ሕዝብ ከፋብሪካ እንደሚወጣ ወጥ ምርት አይደለም። የተለያየ ፍላጎት፣ ምርጫና ዝንባሌ ስለሚኖረው። አሥር በመቶ እንኳ ተቃዋሚዎች ቢያሸንፉ መሬት ላይ ያለውን ሀቅ አያንፀባርቅም። የፌዴራሊዝም ባለሙያዎችና አገራዊ የውክልና ተቋማት ሕዝቡ ውስጥ ያሉ ልዩነቶችን ማንፀባረቅ አለባቸው ይላሉ። ስለዚህ ኢሕአዴግ አሽነፍኩ ያለበት ሒደትም የታወጀው ውጤትም አስቂኝ ብቻ ሳይሆን አደገኛም ጭምር ነው። ውጤቱ ሲነገር ስቀን ነበር፡፡ አሁን ደግሞ አደጋው ፈጦ እያየነው ነው። ኢሕአዴግ ማሸነፍ አይችልም ነበር እያልኩ አይደለም፡፡”

አርበኝነት እና አርበኞች (ኤፍሬም እሸቴ)

 ኲሉ ጻድቅ በጊዜ ርቱዕ” እንዲሉ የአገራችን ሊቃውንት “በደግ ጊዜ ሁሉ ጻድቅ ነው”። በሰላም ጊዜ ሁሉ ጀግና ነው። በደግ ዘመን ሁሉ ሃይማኖተኛ ነው። በጥጋብ ዘመን ሁሉ ቸር ነው። በደስታ ዘመን ሁሉ ወዳጅ ነው። በጤና ዘመን ሁሉ ጓደኛ ነው። ጊዜ ሲገለበጥስ? ስለ እምነቱ ሰው መከራ በሚቀበልበት ዘመን ሰማዕት ለመሆን የሚፈቅደው ጥቂት ነው። በጦርነት ወቅት ጀግናው ትንሽ ነው። በረሀብ ዘመን አዛኝ ሰው ጥቂት ነው። በሐዘን ጊዜ ወዳጅ ማግኘት ከባድ ነው። ጤና ሲርቅ እና በሽታ ሲመጣ የሚደግፍና ቀና የሚያደርግ ማግኘት ከባድ ነው። ማዕበሉ ይዞህ ሲነጉድ እጁን የሚያቀብልህ ከየት ታገኛለህ? ማርክ ትዌይን እንዲህ አለ፦ “In the beginning of a change, the patriot is a scarce man, and brave, and hated and scorned. When his cause succeeds, the timid join him, for then it costs nothing to be a patriot” ― (Mark Twain) አፍታትቼ ስተረጉመው “በለውጥና በነውጥ ወቅት፣ አርበኛ ውድ ነው። አርበኛ ጀግና ነው። ግን ማንም አይወደውም። ሁሉም ፊቱን የሚቋጥርበት ሰው ነው። አርበኛው ያነገበው ዓላማ ሲሳካ ግን የጠሉት ሁሉ ይከቡታል፤ ከዚያ ወዲያማ አርበኛ መሆን ዋጋ ስለማያስከፍል ሁሉ አርበኛ ይወዳል፤ አርበኛ ይሆናል” እንደማለት ነው። አርበኝነት ጀግንነት ነውና አርበኞች በቀላሉ አይገኙም። ግንባራቸውን ለጥይት፣ ደረታቸውን ለጦር፣ ጀርባቸውን ለግርፋት ያዘጋጁ ሰዎች አርበኞች ናቸው። ነገር ግን እነርሱ በጥይት አረር ለሚመቱት፣ እነርሱ በጦር ለሚወጉትና ለሚገረፉት ሐሳባቸው ብቻ የሚያስፈራቸው ብዙዎች ናቸው። አርበኝነት በሐሳብ ደረጃ ቢወደድም በየዘመኑ የነበሩ አርበኞች ግን ይወደዱ ነበረ ማለት አይቻልም። አርበኛው የሚወደደው እርሱ የቆመለትና የሞተለት ዓላም ሲሳካ ብቻ ነው። ያን ጊዜ በከንፈር መጠጣ፣ በዘፈን ድርደራ፣ በመቃብር ሙሾ የሚያመሰግነው አያጣም። በቁሙ የገፋው ሲሞት ያነሣዋል። አጼ ቴዎድሮስ እጅግ የተደነቀ ንጉሥ ነው። (ነገሥታት አጼ ዮሐንስ፣ ምኒልክ ወይም ኃ/ሥላሴ አንቱ ናቸው። ለምን ቴዎድሮስን ብቻ “አንተ” እንደምንል አላውቅም። ምናልባት ሞገደኛ ስለሆነ ይሆን ወይስ “የኮሶ ሻጭ ልጅ” የሚለውን ተቀብለነው? ለነገሩ እንኳንስ ቴዎድሮስን እግዜርንም አንተ ስለምንለው በፍቅር ትርጉሙ ወስጄዋለሁ።) “መቅደላ አፋፉ ላይ ጩኸት በረከተ፣ የሴቱን አናውቅም ወንድ አንድ ሰው ሞተ” እንበለው እንጂ መጀመሪያውኑ ብቻውን እንዲሞት ፈርደንበት ነበር። እንግሊዞቹን መርተን መቅደላ ተራራ ግርጌ ያደረስናቸው እኛው ነን። አገር ምድሩን ገዝተን (ዝ ይጠብቃል) ሰው እንዳይከተለው ያደረግን እኛው ነን። ሲሞት በዘፈን ያሞገስነውም እኛው ነን። “ወንድ ማን እንደ በላይ” እንበል እንጂ በላይ ዘለቀ መሐል ከተማ ሲሰቀል ማንም አልታደገውም። “ተሰቀለ ሲሉኝ ዝናሩ ነው ብዬ፣ ተሰቀለ ሲሉኝ ጠመንጃው ነው ብዬ፣ ለካስ በላይ ኖሯል ትልቁ ሰውዬ” ብለን አለቀስን። አበቃ። አምስት ዓመት በዱር በገደሉ የተንከራተቱ አርበኞች አገራቸውን ነጻ አወጡ። እሰየው። ባንዶቹም ይጸየፉት የነበረውን አርበኝነት አሞገሱ። “ኢትዮጵያ አገሬ ሞኝ ነሽ ተላላ፤ የሞተልሽ ቀርቶ የገደለሽ በላ” ብለን አዜምን። አርበኞቹ ከነጻነት ማዕዱ ተገለሉ፣ የአብዮት ሰማይ እስኪደፋባቸው ድረስ ባንዳዎቹ ተሞገሱ። ድሮስ አርበኝነትን ማን ይጠላል፤ አርበኛን እንጂ። አርበኝነትን እያሞገስን፣ አርበኛውን እያገለልን፣ ለነጻነት የደማውን ትተን ስለ ነጻነት እንዘምራለን። አርበኝነት የሚጠይቀው ውድ ዋጋ ሕይወትን መገበር ከሆነ ከጥንት እስከዛሬ ይህንን የፈጸሙ አሉ። ይብዛም ይነስም በአምስት ዓመቱ የጠላት ወረራ ወቅት የተዋደቁት ብቻ በጅምላ ስም “አርበኞች” ይባሉ እንጂ አርበኝነትና አርበኞች እንደየዘመኑና በየዘመኑ አሉ። የኢትዮጵያ ድንበር የታጠረው በአርበኛ አጥንት ነው። አገሪቱ “ዳሩ እሳት መሐሉ ገነት” ሆና ከኖረች እሳቱ በበላቸው ሰዎች ደምና አጥንት እንጂ በሌላ በምን ይሆናል። ከአርበኝነት ሁሉ ዳሩ እሳት በተባለው የጦርነት አውድማ የሚውሉትን እንጂ መሐሉ ገነት በተባለው ሥፍራ የሚኖሩትን የየዘመናችንን አርበኞች ማስተዋል ችለን ይሆን? የሚከፍሉትን ዋጋስ ማን ይረዳላቸው? የአርበኛ ኑሮና ሕይወት ምኑ ይማርካል? ሕይወትን ለአደጋ ማጋለጥ፣ ከራስ አልፎ የራስ ወገንን ኑሮ ማናጋት። አምስት ዓመት በዱር በገል ከመዋጋት ከጣሊያኑ ጋር ወግኖ መኖር አለ አይደል? ዛሬስ ቢሆን ብረት ያነገበውን ተቃውሞ በማዕከላዊ እስር ቤት ከመንገላታት ገዳዩን ጻድቅ፣ ሌባውን ለጋስ፣ ቀጣፊ ውሸታሙን እውነተኛ አድርጎ በመናገር መኖር ይቻል የለ? አርበኝነት ደስ ይላል። የአርበኛ ዕጣ ፈንታ ግን ያስፈራል። ባንዳነት ያሳፍራል ባንዳ መሆን እና የባንዳ ኑሮ ግን ያስጎመጃል። ባንዳው ራሱ ቢጠየቅ ባንዳነትን ያወግዛል። ባንዳ ለምን እንደሆነ ቢጠየቅን ግን ምክንያት አያጣለትም። “ንጉሡ ራቁታቸውን ናቸው” ከማለት ይልቅ “የንጉሡ ልብስ ያምራል” የሚለው ቢጠየቅ ውሸታምነትን ይኮንናል። ለመዋሸቱ ለራሱ ውሸት ግን ምክንያት አያጣለትም። ታዲያ አርበኞችን ማን ይወዳል? መከራን ማን ይናፍቃል። በአርበኝነት ጀምረው በባንድነት የሚጨርሱ ሰዎችን ታሪክ ልብ ብለን ካስተዋልን ምክንያቱን እንረዳዋለን። ስለ መብት መከበር ይጮኹ የነበሩ ተገልብጠው ለመብት መከበር የሚጮኹትን የሚያስሩ ሲሆኑ አይተናል። ስለ ነጻነት በመጻፍ ጀምረው አሁን ነጻነትን የሚገፍፉትን ሰዎች የሚያሞካሹ ሰዎች እናውቃለን። እነዚህም ቢሆኑ ግን አርበኝነትን አይጠሉም አርበኛ ግን አይወዱም። በአርበኛው ውስጥ የራሳቸውን ባንዳነት ያያሉና። ኢትዮጵያ ውስጥ ጋዜጠኛ መሆን ወይም ከመንግሥት ተቃራኒ የሆነ ፖለቲካ የሚያራምድ ሰው መሆን አርበኝነት ይጠይቃል። መዘዙን እያየነው ነውና። ጋዜጠኛም ሆነ ፖለቲከኛ ባትሆን ነጻ ሰው መሆንም አርበኝነት ነው። ኅሊናን ዳኛ አድርጎ መኖር፤ ክፋትን መጥላት፣ ከመልካም ጋር መተባበር፣ ለደሃው ማዘን፣ አገርን መውደድ፣ ያልሰሩበትን ገንዘብ አለመፈለግ፣ ዘረኝነትን መጠየፍ አርበኝነት ነው። ባንዳነት በየዘመኑ አለ ካልን በዚህ ዘመን ያለው ባንድነት ከሚሞተው ሰው ይልቅ ለገዳዩ ማዘን፣ የአገዳደሉን ትክክለኛነት ለማሳመን ደፋ ቀና ማለት ነው። ገዳይማ ከሞተው ሰው ሕይወት ይልቅ ለመግደል ስለጠፋው ጥይት መቆርቆሩ የታወቀ ነው። በዚህ ዘመን ከአስኮ እስከ አሶሳ፣ ከደብረ ዘይት እስከ ሐሮማያ ድምጻቸውን የሚያሰሙ ልጆች አርበኝነት ያስገርመኛል። አንዲት ወረቀት በጻፉ እጃቸው በካቴና የሚታሰሩት ጦማርያን እና ጋዜጠኞች የሚከፍሉት ዋጋ ልቤን ይገዛዋል። ብረት ካነገበው ደፋር ነኝ ባይ ይልቅ በፈገግታ አንገታቸውን ደፍተው በየፍርድ ቤቱ የሚቆሙት ሰዎች ጀግንነት ያስደንቀኛል። ሁለት ጸጉር አብቅሎ ገራፊዎችን ከሚያሰማራው ሽማግሌ ይልቅ ግርፋቱን ለሚታገሱት ወጣቶች ክብር አለኝ። በብዙ ወንጀል ከተበላሸ አረጋዊነት ይልቅ በንጽሕና የተጌጠ ወጣትነት ይማርከኛል። "ሰነፍ ዝም ቢል ጠቢብ ሆኖ ይቈጠራል፥ ከንፈሩንም የሚቈልፍ 'ባለ አእምሮ ነው' ይባላል።" (መጽሐፈ ምሳሌ 17፥28) እንዲል እያዩ እንዳላዩ፣ እየሰሙ እንዳልሰሙ ከሚሆኑ “አዋቂዎች” ይልቅ “ጆሮ ያለው ይስማ” እያሉ በበረሃ የሚጮሁ ሰዎች ያስደንቁኛል። ይቆየን - ያቆየን ይህ ጽሑፍ አዲስ አበባ ለሚታተመው የአዲስ ጉዳይ መጽሔት የተጻፈና በዚያም ላይ ለሕትመት የበቃ ነው።http://www.ethioreference.com/amharic/arbegnenet.pdf

Saturday, May 28, 2016

የኢህአዴግ መንግስት ወታደራዊ ሃይሉን ለማጠናከር የጦር መሳሪያዎችን በብዛት እየሸመተ ነው


ግንቦት ፲፯ (አሥራ ሰባት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የመከላከያ ሰነዶች እንደሚያመለክቱት ካለፉት 2 አመታት ጀምሮ የኢህአዴግ መንግስት ከፍተኛ የሆነ ወጪ በማውጣት የጦር መሳሪያዎችን እየገዛ ሲሆን፣ የጦር መሳሪያ ባለሙያዎችንም ወደ ቻይናና ሌሎች የምስራቅ አውሮፓ አገራት በመላክ እያሰለጠ ነው።
ሰነዶቹ እንደሚያስረዱት በሁለት አመታት ውስጥ መንግስት ለታንክ መግዢያ ብቻ ከ684ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ያደረገ ሲሆን፣ ለመድፎች 896 ሚሊዮን ብር፣ ለተሽከርካሪዎች ፣ ለተለያዩ ጠመንጃዎች፣ ለቦንቦችና ለመሳሰሉት ወታደራዊ ቁሳቁሶች ደግሞ ከ2 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ አድርጓል። ይህ አሃዝ ከመስከረም 11፣ 2005 ዓም እስከ 2007 ዓም ያለውን ጊዜ ብቻ የሚመለከት ነው።
በብዛት የገቡት የጦር መሳሪያዎች ሩስያ ሰራሽ የሆኑ ቲ- 172 የሚባሉ ታንኮችና 122 ሚሊሜትር መድፎች ናቸው።

በዛሬው የማዕደ-ኢሳት ዝግጅታችን ፦”እንደ ልማዴ ሰክሬ መጣሁ”፣ ሰው የዘራውን ያንኑ ያጭዳል- የላይቤሪያና የኢትዮጵያ መሪዎች ዕጣ በአጭሩ፣


………ዳኛ ብርቱካን ሚዴቅሳ እንድትፈታ ከወላጅ እናቷ ጀምሮ አቤቱታ የቀረበላቸው አቶ መለስ ዜናዊ በወቅቱ የሰጡት ምላሽ፦”በሊማሊሞ በኩል ማቋረጥ ይችላሉ!” የሚል ነበር።እናም እንደፎከሩት ዕድሜ ልክ አስፈረዱባት። ሆኖም ከወራት በኋላ ብርቱካን ከሀቫርድ ዩኒቨርሲቲ ተመርቃ ስትወጣ አቶ መለስ እስከወዲያኛው አሸልበዋል። አቡነ ቄርሎስ፦”ገልጦ የሚያነበው የለም እንጂ ሞት ታላቅ መጽሐፍ ነው” ቢሉም ፤ቀሪዎቹ ባለስልጣኖች ከመለስ ሞት ሊማሩ አልቻሉም። እንዲሁም ጸሀፊ አንዷለም ቡከቶ ገዳ፦ “ የ23 ቁጥር ነገር” ይለናል። በላይ በቀለ ወያ ዓለምነሽ፣ ካሳነሽ አጠዱን በአጭሩ ያሳየናል። መልካም ቆይታ

“ግንቦት 20፤ደርግን ከማስወገድ የዘለለ ፋይዳ አላመጣም” Written by መታሰቢያ ካሣዬ

አዲስ አድማስ ግንቦት 20 ቀን 2008 ዓ.ም
ባለፉት 25 ዓመታት በዲሞክራሲ ግንባታ፣በሰብአዊ መብት አያያዝና በፍትህ ሥርዓት----የተመዘገቡ ስኬቶችና
ውድቀቶች እንዴት ይገመገማሉ? ግንቦት 20 ለኢትዮጵያውያን ምን ፈየደላቸው? የአዲስ አድማስ ጋዜጠኛ መታሰቢያ
ካሳዬ፤አንጋፋውን የህግ ባለሙያ አቶ አብዱ አሊ ኢጂራን አነጋግራቸዋለች፡፡

እርስዎ ግንቦት 20ን እንዴት ይገልጹታል ?
ግንቦት 20 ትልቅ ቀን ነው፡፡ ትልቅ የሆነው ግን ለውጥ ስለመጣ ሳይሆን ደርግን የመሰለ አፋኝ፣ ጨቋኝ፣ ወንበዴና ወሮበላ መንግስት ስለወደቀ ነው፡፡ ያ ትልቅ ድል ነው፡፡ 17 ዓመት በፈጀ ትግል የተገኘ ድል፡፡ ትግሉ 17 ዓመት የፈጀው በደርግ ግዙፍነት ብቻ ሳይሆን ህዝቡን አሰባስቦ ትግሉን የሚመራ በመጥፋቱ ጭምር ነው፡፡ ከዚህ በላይ ግን የለውም፡፡ ከዚህ በላይም አይደለም፡፡ 
የግንቦት 20 ትልቁ ፋይዳ፣ደርግን መገላገሉ እንጂ አዲስ ነገር ማምጣቱ አይደለም፡፡  ደርግን ከማስወገድ በላይ ሰፍቶ የሄደ ለውጥ አላሳየንም፡፡
 ህዝቡ የደርግን መውደቅ የፈለገው በምትኩ ወይም በደርግ መቃብር ላይ የተሻለ ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት፣ ነፃነትና ፍትህን አገኛለሁ ብሎ ነው፡፡ ሆኖም በእያንዳንዱ ጉዳዮች ላይ የሚፈለገውን ያህል መራመድ አልተቻለም፡፡ 
የተሻለ ሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ፣ ከጎረቤቶቿ ጋር በሰላም የምትኖር አገር መመስረት ነበር ግቡ፡፡ ይህ ሁሉ ተሟልቷል ወይ? ካልሽኝ አንፃራዊ መሟላት አለ፡፡ ከኤርትራ ጋር ያለን ግንኙነት ያው ነው፡፡
 ጦርነቱ ቢያቆምም፣ ጦርነት የሌለበት ሰላምም የሌለበት ሁኔታ ነው ያለው፡፡ ጉዳያችን ወይም ፋይላችን አሁንም አልተዘጋም፡፡ 
ህአዴግ ከአምባገነኑ የደርግ ሥርዓት በእጅጉ የተሻለ መሆኑን በተደጋጋሚ ሲገልጽ ይሰማል፡፡ እርስዎ ንጽጽሩን እንዴት ያዩታል?
ኢህአዴግ ሁልጊዜም ራሱን የሚያወዳድረው ከደርግ ጋር ነው፡፡ ይህ በጣም አሳዛኝና አስተዛዛቢ ነገር ነው፡፡ እንዴት አንድ መንግስት፣ 17 ዓመት ሙሉ ከታገለው መንግስት ጋር ራሱን አወዳድሮ፣ እኔ እሻላለሁ ብሎ ይናገራል? እንዴት አንድ መንግስት፣ ራሱን ከኤርትራ መንግስት ጋር አወዳድሮ የተሻልኩ ነኝ ይላል? በእርግጥ ደርግ በመውደቁ ምክንያት ሰላም አለ፡፡ የመን ወይም ሶሪያና ኢራቅ ውስጥ ያለው ችግር እኛ ጋ የለም፡፡ 
ይህ ግን ደርግ በመውደቁ ምክንያት እንጂ ኢህአዴግ በመምጣቱ ምክንያት የጨመረው ነገር ኖሮ አይደለም፡፡ አንዳንድ ጊዜ እንደውም ደርግ ራሱ ተፈቅዶለት ቢኖር ኖሮ፣አሁን አለም ሁሉ ተቀይሮና ተለዋውጦ ባለበት ሁኔታ፣ ይህን ያህል መራመድ ያቅተዋል ብዬ አላስብም፡፡ አንዳንድ ሰዎች ይህን በመናገሬ ሊበሳጩ፣ ሊናደዱና ሊያብዱ ይችላሉ፤እውነቱ ግን ይሄ ነው፡፡ 

የህወሃት ድል 25ኛው ዓመት ሲከበር May 28, 2016


def-thumb
ህወሃት ለንግሥና የበቃበትን 25ኛ ዓመት ለማክበር ከ2 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ መድቦ ከገጠር ቀበሌ እስከ አገሪቱ ዋና ከተማ ነዋሪ የሆነውን ህዝብ በየሥርቻው ባዘጋጀው የፈንጠዝያ ድንኳን እንዲሰባሰቡለትና በዓሉን እንዲያደምቁለት በተለያዩ መንገዶች ሲያስገድድ ሰንብቶአል። “የግንቦት 20 ድል ባስገኘልን ዕድል ተጠቅመን ለዚህ ወይም ለዚያ ስኬት በቃን” የሚሉ ጥቂቶችን በቴለቪዥንና በሬዲዮ ከማቅረብ አልፎም ለቱባ ቱባ ባለሥልጣናቱና በግል ጥቅም ተጠልፈው በዙሪያው ለተሠለፉ ወፋፍራም ሎሌዎቹ ያሠራውን የኢህአደግ ባንዲራ አልብሶ በትላልቅ አዳራሾች በማጨቅ የ25ቱን አመት ገድል እየሰበከ ጣራው እስኪሰነጠቅ ሲያስጨበጭባቸውም ከርሞአል።
ሁለት ቢሊዮን ብር ማለት 100 /አንድ መቶ/ ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ማለት ነው። 20/ሃያ/ ሚሊዮን ህዝብ አስቸኳይ የምግብ ዕርዳታ ካላገኘ በቀር ህይወቱ ከፍተኛ አደጋ ላይ እንደሚወድቅ በመስጋት አለም አቀፍ ለጋሽ አገሮች ከግብር ከፋይ ህዝባቸው በሰበሰቡት ገንዘብ የዕርዳታ እህል ሸምተው ለማቅረብ በሚራወጡበት በዚህ የመከራ ሰዓት 100 /አንድ መቶ/ ሚልዮን ዶላር ከመንግሥት ካዝና ወጭ አድርጎ በዓለ ንግሥና ማክበር በአገርና በህዝብ ላይ የሚሠራ ጭካኔ የተሞላበት ከፍተኛ ወንጀል መሆኑ ብዙ አያጠያይቅም። እንዲህ ዓይነት ጭካኔ የተሞላበት ወንጀል ደግሞ ለህወሃት አዲስ ነገር አይደለም።

ጥብቅ መረጃ... የጆሐንስበርግ ዲያስፖራ በሽብርተኛነት ተወንጅሎ ተያዘ!




ዛሬ ኮሽታዎች ሁሉ ያስበረግጡታል! ከምንም በላይ በሰፊዉ የኢትዮጵያ ህዝብ ላይ ያደረሰዉ ወንጀል ነግ በምን አይነት መልኩ እንደሚከፈለዉ ሲገምት ሰላም ይነሳዋል፤ ከንፈር ያልነከሰበት ልቡ ያላቄመበት በእርሱ በግፍ ያልተነካካ ባለመኖሩ ሁሉንም እየነከሰ በማቁሰል ዉድቀቱን እያፋጠነ ይገኛል! 
አዎ እራሱን ህወሃት እያለ የሚጠራዉ የክፉዎች ስብስብ የሆነዉ የህዝብ ጠላት ወያኔ የሚመራዉ የብሔራዊ መረጃ ከኢትዮጵያ ዉጭ ወደ ሐገር ቤት የሚገቡ ኢትዮጵያዊያንን በማንገላታት በማሰርና በማፈን በእጅጉ ተጠምዷል፡ በመሆኑም ከአሜሪካ፣ ከኖርዌይና፣ ከሲዉዲን እንዲሁም ከደቡብ አፍሪካ የሚገቡ ወገኖቻችን የአዲስ አበባ ኤርፖርት ላይ በተቀመጠዉ የዚሁ የብሔራዊ መረጃ ቀኝ እጅ የሆነዉ እና በአንድ ብሔር ብቻ በተመሰረተዉ ኢሚግሬሽን ፖሊስ ቡድን ያለአግባብ እየተንገላቱ ይገኛሉ።
በዚህም የተነሳ በዚህ ባሳለፍነዉ 15 ቀናት ብቻ 2 ሴቶችና 5 ወንዶች የአርበኞች ግንቦት 7 እና የኦነግ አባል ናችሁ ተብለዉ ከአዲስ አበባ ኤርፖርት ተጠልፈዉ በሽብር ወንጀል ተከሰዋል! ከነዚህም መካከል ሙሉጌታ የተባለ ከየትኛዉም የፖለቲካ ድርጅት ጋር ግንኙነት የሌለዉ ነዋሪነቱ በደቡብ አፍሪካ የሆነና ጆሐንስበርግ ሞል በተባለ የንግድ መአከል ዉስጥ በአነስተኛ እና ጥቃቅን ስራ ላይ የተሰማራ ግለሰብ በነዚሁ ወንጀለኛና የወያኔ ቡድኖች እጅ መዉደቁን ምንጮች ጠቁመዋል። 
ሙሌጌታ ከጆሓንስበርግ ኦሊቨር ታምቦ ኢንተርናሽናል ወደ አዲስ አበባ ከገባበት ወቅት አንስቶ የብሔራዊ መረጃ ቡድን አባላቶች ግለሰቡን ሲከታተሉት እንደነበረ ምንጮች የጠቆሙ ሲሆን በተለይም በወያኔ ቀንደኛ ደጋፊዎች እና በትግራዩ ቡድን ኢንባሲ ደቡብ አፍሪካ አዲስ የተቋቋመዉ የዲያስፖራ ኢንጌጅመንት አሶሴሽን ደቡብ አፍሪካ ( Diaspora engagement association in south Africa ) የተባለ መሐበር ስለ ግለሰቡ ለወያኔ የብሔራዊ መረጃ የሰጠዉ የተሳሳተ ማንነት ምክንያት ግለሰቡ እንዲታፈንና በትናንትናዉ እለት የአርበኞች ግንቦት 7 አባል እንዲሁም ለደቡብ አፍሪካ አርበኞች የግንቦት 7 አባላቶች መልእክት ይዞ ሲሄድ ተያዘ በሚል የሐሰት ክስ በሽብር ወንጀል ተከሶ ዘብጥያ ተወርዉሯል።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ ! !
( ጉድሽ ወይኔ )

Nine year old daughter of Andargachew Tsige sues the UK government ESAT News (May 27, 2016)


The daughter of Andargachew Tsige, kidnapped by the Ethiopian regime in 2014 at Yemeni airport and in death row in Ethiopia has sued the British government, according to Reprieve, an organization that’s campaigning for his release.
“Lawyers for Menabe Andargachew, 9, a joint US-UK citizen living in London, have begun judicial review proceedings against the British Foreign Office over ministers’ handling of the case of her father, Andargachew ‘Andy’ Tsege,” the report said.
Minabe “has launched legal action against the UK Government, for its refusal to request his return,” said Reprieve.
"My mom said he's been sentenced to death," Menabe told NBC News as her chin quivers. "I just don't know if we can get him back in time."
The UN’s Human Rights Council’s Working Group on Arbitrary Detention and the European Parliament have previously called for Mr. Tsege’s release, as have US members of Congress. In a statement published today by NBC News, Senator Ben Cardin, who sits on the US Foreign Relations Committee, said “Mr. Tsege’s grave case is one of many that gives cause for concern.”
(Photo by Cassandra Vinograd / NBC News)

የህወሃት ድል 25ኛው ዓመት ሲከበር



ህወሃት ለንግሥና የበቃበትን 25ኛ ዓመት ለማክበር ከ2 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ መድቦ ከገጠር ቀበሌ እስከ አገሪቱ ዋና ከተማ ነዋሪ የሆነውን ህዝብ በየሥርቻው ባዘጋጀው የፈንጠዝያ ድንኳን እንዲሰባሰቡለትና በዓሉን እንዲያደምቁለት በተለያዩ መንገዶች ሲያስገድድ ሰንብቶአል። "የግንቦት 20 ድል ባስገኘልን ዕድል ተጠቅመን ለዚህ ወይም ለዚያ ስኬት በቃን" የሚሉ ጥቂቶችን በቴለቪዥንና በሬዲዮ ከማቅረብ አልፎም ለቱባ ቱባ ባለሥልጣናቱና በግል ጥቅም ተጠልፈው በዙሪያው ለተሠለፉ ወፋፍራም ሎሌዎቹ ያሠራውን የኢህአደግ ባንዲራ አልብሶ በትላልቅ አዳራሾች በማጨቅ የ25ቱን አመት ገድል እየሰበከ ጣራው እስኪሰነጠቅ ሲያስጨበጭባቸውም ከርሞአል።

ሁለት ቢሊዮን ብር ማለት 100 /አንድ መቶ/ ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ማለት ነው። 20/ሃያ/ ሚሊዮን ህዝብ አስቸኳይ የምግብ ዕርዳታ ካላገኘ በቀር ህይወቱ ከፍተኛ አደጋ ላይ እንደሚወድቅ በመስጋት አለም አቀፍ ለጋሽ አገሮች ከግብር ከፋይ ህዝባቸው በሰበሰቡት ገንዘብ የዕርዳታ እህል ሸምተው ለማቅረብ በሚራወጡበት በዚህ የመከራ ሰዓት 100 /አንድ መቶ/ ሚልዮን ዶላር ከመንግሥት ካዝና ወጭ አድርጎ በዓለ ንግሥና ማክበር በአገርና በህዝብ ላይ የሚሠራ ጭካኔ የተሞላበት ከፍተኛ ወንጀል መሆኑ ብዙ አያጠያይቅም። እንዲህ ዓይነት ጭካኔ የተሞላበት ወንጀል ደግሞ ለህወሃት አዲስ ነገር አይደለም። የዛሬ 25 ዓመት የቤተመንግሥት ሥልጣን ከመቆጣጠሩ ስድስት ዓመት ቀደም ብሎ ተከስቶ በነበረው የ1977 ረሃብ ወቅት እንደቅጠል ይረግፍ ለነበረው የትግራይና የሰሜን ወሎ ህዝብ ከአለም አቀፍ ለጋሾች በሱዳን በኩል የተላከውን የነፍሥ አድን እህል አሳልፎ በመሸጥ አሁን ለድግስ የመደበውን ያህል ገንዘብ ለትጥቅ መሣሪያ መግዣ አውሎታል። በዚያን ወቅት አመራር ላይ የነበሩና በድርጊቱ አዝነው ከድርጅቱ የለቀቁ አባላቱ እንደሚናገሩት በረሃብተኛው ህይወት ተፈርዶ በተገኘ ገንዘብ የተሸመተው የጦር መሣሪያና የሎጄስቲክ መገልገያ ህወሃትን ለድል ለማብቃት ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርጎአል። በዚህም የተነሳ ረሃብ ህወሃት ለሚያከብረው የግንቦት 20 ድል ባለውለታ ነው። ህወሃት ሥልጣን ከተቆጣጠረ ወዲህ በአገራችን ተከስተው የነበሩ ሌሎች ሁለት የረሃብ አደጋዎችም እንዲሁ ለባለሥልጣናቱ ከፍተኛ የገንዘብ ምንጭ የሆኑበት አጋጣሚዎችን መጥቀስ ይቻላል ። ለአደጋ ጊዜ መጠባበቂያ ተብሎ በአገሪቱ ሃብት ተገዝቶ የተከማቸን ብዙ ቶን እህል ለጋሽ አገሮች ለተራበው ወገናችን በውጪ ምንዛሪ ገዝተው እንዲያድሉት በማድረግ በሚሊዮን የሚቆጠር ሃብት ህወሃቶች ኪስ እንዲገባ ተደርጎአል። ህወሃት 25ኛ የድል አመቱን ሞቅ ደመቅ ባለ አከባበር ለማክበር በዚህን ወቅት ይህንን ያህል ገንዘብ ሲመድብ ለጋሾች ለ20 ሚልዮን ረሃብተኛ ወገናችን ለማቅረብ ከሚሯሯጡት ገንዘብ የሚያገኘውን ወደር የለሽ ትርፍ በሆዱ እያሰላ እንደሆነ መገመት አይስቸግርም ።

Friday, May 27, 2016

“ህዝቡ ከኢህአዴግ መሪዎች ይልቅ በውጭ ለሚገኙ የፖለቲካ መሪዎች እውቅና እየሰጠ ነው” ሲል የደህንነት መስሪያ ቤቱ አስታወቀ


ግንቦት ፲፱ (አሥራ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ኢህአዴግ 25ኛ አመት በአሉን እያከበረ በሚገኝበት ወቅት እያደረገ ባለው ግምገማ የደህንነት መስሪያ ቤቱ ለስርአቱ አደጋ ሊፈጥሩ ይችላሉ ያላቸውን ጉዳዮች ለውይይት ከማቅረብ ባሻገር ፣ ህዝቡ በአገር ውስጥ ላሉ የኢህአዴግ ባለስልጣናት ከሚሰጠው እውቅና ይልቅ በውጭ አገር ለሚገኙ የተቃዋሚ መሪዎች እየሰጠ በመምጣቱ የስደት መሪዎችን እስከመሾም ተደርሷል ብሎአል ።

አቶ መለስ ዜናዊ ለትውልድና ለሀገራችን ጥለውት ያልፉት እኩይ፣ መራራና አሳዛኝ ሀቆች

ከፊልጶስ
Forcing people to mourn Meles Zenawi's death in Ethiopiaየአቶ መለስ፣ የኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊያን  ግንኙነት ሁሌም ይደንቀኛል። በሀገርና በትውልድ ላይ የፈጸሙትንና ጥለውት የሄዱትን ከትውልድ ወደ ትውልድ ይሚትላልፍ መርዝ ሳስብ፤
Forcing people to mourn Meles Zenawi's death in Ethiopia
 ለኢትዮጵያና ለኢትዮጵያዊያን  የነበራቸውን ጥላቻ ስቃኝ ፤ በ’ርግጥ የሰው አዕምሮ ተመራምሮ ይደርስብት ይሆን? እላለሁ። አሁንም ከኢትዮጵያና ከዚች ዓለም ተለይተው ሄደው ግፋቸውን ሳስታውስ  እጅግ አድርጎ ይገርመኛል ። ዘፋኙ ምን ነበር ያለው?……

’’….ግርም ያደርገኛል ያሰበኩት እንደሆን
ሰው በገዛ ሀገሩ ስደተኛ ሲሆን።….”
እስቲ ባለፉት አመታት አቶ መለስ  በኢትዮጵያና በኢትዮጵያዊያን ላይ የሰሩትንና የፈጸሙትን መራራ ሀቆችና ለዚህ ትውልድ ጥለውት ያለፉትን ታሪክ እጅግ ባጭር ባጭሩ (የውቅያኖስን ውሀ በጭልፋ ጨለፎ ለመጨረስ እንደመሞከር ይቆጠራል።) እናስታውስ።
1አቶ መለስ፣ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነታቸው፤
አቶ መለስ ዜናዊ በኢትዮጵም ሆነ በኢትዮጵያዊነታቸው አያምኑም ነበር። ”ኢትዮጵያዊ ነኝ” ወይም ”ኢትዮጵያ ሀገራችን” ወይም ”ሀገሬ” ሲሉ ተሰምተው አያውቁም።

ኢህአዴግ “ህዝቡን በመልካም አስተዳደር ማወያየታችን አመጽ እንዳይፈጠር አድርጓል” አለ


ግንቦት ፲፰ (አሥራ ስምንት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- 25ኛ ዓመት የስልጣን ዘመኑን በማክበር ላይ ያለው ኢህአዴግ፣ ከፍተኛ አመራሮቹን ይዞ ግምገማ በማድረግ ላይ ነው። በግምገማው ኢህአዴግ ባለፉት 25 አመታት የተጓዘባቸው መንገዶች እና ያጋጠሙት ችግሮች በነባር አመራሮቹ ውይይት ተደርጎባቸዋል። ከአቶ መለስ ዜናዊ ሞት በሁዋላ የኢህአዴግን የርእዮት አለም አቅጣጫ በማብራራት ግንባር ቀደም ሆነው የወጡት በሁዋላም ከጤና ጋር በተያያዘ የመድረክ እንቅስቃሴያቸውን የቀነሱት አቶ በረከት ስምኦን በግምገማው መሪ ተዋናይ ሆነው ወጥተዋል።

የአውሮፓ ህብረት በኢትዮጵያ ስላለው የዴሞክራሲ ችግር ከኢትዮጵያ ባለስልጣናት ጋር እየተወያየሁ ነው ኢሳት (ግንቦት 18 ፥ 2008)


በኢትዮጵያ ባለው የሰብዓዊ መብት ጥሰትና የዴሞክራሲ ችግሮች ላይ ዝምታን መርጧል የሚል ትችል እየቀረበበት ያለው የአውሮፓ ህብረት በሃገሪቱ ያለውን ችግር በተለያዩ መድረኮችና ከባለስልጣናት ጭምር በመግለጽ ላይ መሆኑን አስታወቀ።
በቅርቡ በኢትዮጵያ ጉብኝትን ያደረጉና ከጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ሃይለማሪያም ደሳለኝ ጋር በሃገሪቱ ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ የመከሩት የሃገሪቱ የፓርላማ አባላት “ትክክለኛ የሆነ አመራር በአፈና ላይ የተመሰረተ መሆን የለበትም” ሲሉ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ በአካል ቅሬታቸውን መግለጻቸውንም ይፋ አድርገዋል።
በአውሮፓ ፓርላማ ካሉ የፖለቲካ ተወካዮች መካከል ዋነኛ የሆነው የሶሻሊስትና የዴሞክራቲክ ጥምር ፕሬዚደንት የሆኑት ጅያኔ ቲፔላ ህብረቱ በኢትዮጵያ ያለውን የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች በተመለከተ ዝምታን አለመምረጡና ጉዳዩን በልዩ ሁኔታ እየተከታተለው እንደሆነ አዲስ ስታንዳርድ ከተሰኘ መጽሄት ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ አስረድተዋል።
እንደሌሎች የአፍሪካ ሃገራት ሁሉ በኢትዮጵያ ያለውም የልማት እንቅስቃሴ ከዴሞክራሲ ተለይቶ የሚታይ ጉዳይ አለመሆኑን ሃላፊው ገልጸዋል።
የአውሮፓ ህብረት ሽብርተናነትን ለመዋጋት በሚል በኢትዮጵያ ያለውን የሰብዓዊ መብት ጥሰትን ችላ ብሎታል ተብሎ ስለሚቀርቡ ቅሬታዎች የተጠየቁት ጂያኒ ቲፔላ በሃገሪቱ በመገናኛ ብዙሃን የፖለቲካ አመራሮች ላይ የተወሰዱ የእስር ድርጊቶችን በአደባባይ በማውገዝና ስጋታቸውን በመገለጽ ላይ መሆናቸውን አስታውቀዋል።

Thursday, May 26, 2016

ጋዜጠኛው አበበ ገላው ያደረገውን በፌስቡክ ጠቅሰህ ሕዝብን ለማነሳሳት ተጥቅመህበታል በሚል በሽብር ተከሰሰ

Negere-Ethiopia-edtor-Getachew-Assefa-300x200.jpghttp://www.zehabesha.com/amharic/archives/61354
የኦሮሚያ ተማሪዎች አመጽ በተቀጣጠለበት ሰሞን መንግስት አስሮ ለረዥም ጊዜ ክስ ሳይመሰርትበት የቆየው ጋዜጠኛ ጌታቸው ሽፈራው በፌደራሉ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ጋዜጠኛ አበበ ገላው ያደረገውን አድንቀህ ሕዝብን ለማነሳሳት ተጠቅመህበታል እና ከኢሳት ጋዜጠኛ ፋሲል የኔዓለም ጋር በፌስቡክ እና በስልክ አውርተሃል በሚል የሽብርተኝነት ክስ ቀረበበት::
እንደ ክሱ ዝርዝር ከሆነ
“ተከሳሽ (ጋዜጠኛ ጌታቸው ሽፈራው) በሚጠቀምበት ማህበራዊ ድህረገአጽ በተለይም ፌስቡክ አድራሻው ተጠቅሞ በውጭ ሃገር የሚገኝ የሽብር ቡድኑ አመራር እና አባል ከሆነው አበበ ገላው በልደታ ከፍተኛ ፍ/ቤት በጸረ-ሽብርተኝነት አዋጅ ተከሶ በመዝገብ ቁጥር 112546 የጥፋተኝነት ውሳኔ ከተሰጠው ጋር ግንኙነት በመፍጠር በቀን 01/9/2006 ዓ.ም በአቶ መለስ ላይ ያደረገው ተቃውሞ መስቀል አደባባይ ላይ ከሚደረግ አንድ ሚሊዮን ሕዝብ የተሳተፈበት የተቃውሞ ሰልፍ የማይተናነስ ነበር:: አሁንም እንዲሁ ኦባማ ላይ ደግሞታል:: የአቤ ጩኸት ዝም ብሎ ያለመገዛት አንድ ድምጽ ብትሆን ለውጥ እንደምታመጣ በጽኑ የማመን ለውጥ አይመጣም ብሎ በተስፋ መቁረጥ ከመቀመጥ የራስን አስተዋጽኦ ማድረግ የተግባር ሰው መሆን ነው በማለት ከሽብር ቡድኑ አባል ጋር የአመጽ ጥሪ በማስተላለፉ”
የሽብር ክስ ተመስርቶበታል ይላል::

ዛሬም በቦሌ ክፍለከተማ ወራ ጋኑ አካባቢ 2 ሰዎች በፌደራል ፖሊስ ተገደሉ * በርካታ ሰዎች የደረሱበት ጠፋ


  • 872
     
    Share
(ቤታቸው የፈረሰባቸው ወገኖች በአደባባይ እንዲሁም ፌደራል ፖሊሶች አካባቢውን ወረውት)
(ቤታቸው የፈረሰባቸው ወገኖች በአደባባይ እንዲሁም ፌደራል ፖሊሶች አካባቢውን ወረውት)
(ቤታቸው የፈረሰባቸው ወገኖች በአደባባይ እንዲሁም ፌደራል ፖሊሶች አካባቢውን ወረውት)
(ቤታቸው የፈረሰባቸው ወገኖች በአደባባይ እንዲሁም ፌደራል ፖሊሶች አካባቢውን ወረውት)
(ቤታቸው የፈረሰባቸው ወገኖች በአደባባይ እንዲሁም ፌደራል ፖሊሶች አካባቢውን ወረውት)
(ቤታቸው የፈረሰባቸው ወገኖች በአደባባይ እንዲሁም ፌደራል ፖሊሶች አካባቢውን ወረውት)
 በአዲስ አበባ ከተማ በቦሌ ክፍለ ከተማ ስር ባለው ወራ ጋኑ በተባለው አካባቢ የመንግስት ሃይሎች የአካባቢውን ነዋሪዎችን መኖሪያ ቤቶች በማፍረስ ለሃብታሞች መሬቱን እየቸበቸቡት ሲሆን ዛሬም ቤቶቹን ለማፍረስ ከሄደው ግብረሃይል ጋር የነበረው ፌደራል ፖሊስ 2 ሰዎችን መግደሉን የአካባቢው ሰዎች አስታወቁ::
ከስፍራው የሚመጡ መረጃዎች እንደጠቆሙት በዚሁ አካባቢ ሰሞኑን መሬቱን ለባለሃብቶች መሸጡን ተከትሎ ከ6 ሺህ የማያንሱ ቤቶች ህገወጥ ናቸው በሚል ፈርሰዋል::
ፌደራል ፖሊስ ባለፈው ሳምንት እንዲሁ በዚሁ አካባቢ ቤቶችን ሲያፈርስ በህዝቡ ተቃውሞ ሲደርስበት ከ10 በላይ ሰዎችን መግደሉን ዘ-ሐበሻ መዘገቧ የማይዘነጋ ሲሆን ዛሬም ድርጊቱን የተቃወሙና የት ሄደን እንኑር ያሉ ወገኖች ከመደብደባቸውም በተጨማሪ 2ቱ ሲገደሉ ከ20 በላይ ሰዎችም ታፍነው መወሰዳቸውና የት እንደደረሱ እንደማይታወቅ የአካባቢው ሰዎች ገልጸዋል::

Wednesday, May 25, 2016

ከወ/ሮ አዜብ መስፍን ጋር በጥቅም ቁርኝት ስሙ የሚነሳው ሳሊኒ ኮንስትራክሽን የ1.86 ቢሊዮን ፓውንድ ፕሮጀክት ተፈቀደለት


1464162766_25may16-salini-ethiopiaኢትዮጵያ የሚደረጉ የኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶችን ከወ/ሮ አዜብ መስፍን ጋር ባለው የጥቅም ቁርኝት እንዲያሸንፍ እየተደረገ ይሰጠዋል እየተባለ የሚከሰሰው የጣሊያኑ ሳሊኒ ኮንስትራሽክን ተጨማሪ ግድብ እንዲሰራ የ1.86 ቢሊዮን ፓውንድ ስምምነት ተፈራረመ::

አዲስ ሊሰራ በታሰበ የኮያሽ ሃይድሮ ግድብ ፕሮጀክትን እንዲያሸንፍ የተደረገው ሳሊኒ ኮንስትራክሽን ይህን ፕሮጀክት እንዲያሸንፍ በግልጽ የተደረገና ሌሎች ታዋቂ ኩባንያዎችን ያካተተ ጨረታ አለመካሄዱን የሚከሱት የውስጥ ምንጮች አሁንም ይህ ድርጅት እንዲያሸንፍ የተደረገው ከስርዓቱ ሰዎች ጋር ባለው የጥቅም ቁርኝት ነው ይላሉ::
ፕሮጀክቱ 6,000 ሚሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ማጠራቀሚያ ድምጽ መፍጠር 170m-ከፍተኛ ሮለር የተጠቀጠቀ ግድብ የሚያካትተው የኮይሽ ሃይድሮ ግድብ ወደ 6.460 GWh የኤሌክትሪክ ሃይል ያመነጫል:: የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል (EEP) ከአዲሱ ሃይል ማመንጫ ወደ 2,200MW የኤሌክትሪክ ሃይል ለማከፋፈል ያግዘዋል ተብሏል::
ኢትዮጵያ ውስጥ በአሁኑ ወቅት በርካታ አካባቢዎች የኤሌክትሪክ ሃይል በርካታ ችግሮችን እየፈጠረ ሲሆን ሃገሪቱ ግን የመብራት ሃይልን ልለኬንያ; ሱዳና ጅቡቲ እየሸጥኩ ነው እያለች ነው::
የጣሊያኑ ኮንስትራክሽን ኩባንያ (ሳሊኒ) ከዚህ ቀደም በኢትዮጵያ የስምጥ ሸለቆ አካባቢ እያካሄደ በነበረው የግድብ ግንባታ በኢትዮጵያና ኬንያ የድንበር ዙሪያ በሚኖሩ ማህበረሰቦች ላይ የረሃብ አደጋ መፈጠሩን ሰርቫይቫል ኢንተርናሽናል የተሰኘ አለም አቀፍ ተቋም ማስታወቁና በስፍራው በመካሄድ ላይ የነበረው የግድብ ግንባታ የቱርካና ሃይቅ የውሃ መጠን እንዲቀንስ በማድረጉ በሺዎቹ የሚቆጠሩ የካሮ ጎሳ አባላት ለረሃብ መጋለጣቸውን ድርጅቱ ማሳሰቡ እንዲሁም በግልገል ጊቤ ሶስተኛ የሃይል ማመንጫ ግድብ ግንባታ ምክንያት በአካባቢው እያደረሰ ነው ያለውን ጉዳት ለአለም አቀፍ የኢኮኖሚና የትብብር ድርጅት ያቀረበው ሰርቫይባል ኢንተርናሽናል በቱርካና ሃይቅ ላይ ህይወታቸው የተመሰረተ ከ100ሺ በላይ የማህበረሰቡ አባላት ለችግር መጋለጣቸውንም መዘገቡ አይዘነጋም::

ማኅበራዊ እሴት እንደ አገር እንድንኖር ካደረጉን ነገሮች ውስጥ አንዱ እና ዋነኛ መሆኑን በኦስሎ የተደረገ ስብስባ ላይ ተገለጠ (ጉዳያችን ዜና)

የስብሰባው ማስታወቂያ 
unnamed
unnamedበኖርዌይ ዋና ከተማ ኦስሎ ሚያዝያ 29፣2008 ዓም ባባተሪ አዳራሽ በኢትዮጵያውያን የጋራ መድረክ አዘጋጅነት በማኅበራዊ እሴት ላይ ያተኮረ ትምህርታዊ  ውይይት ተደርጎ ነበር።በውይይቱ  ላይ የኢትዮጵያ ማኅበረሰብ በኖርዌይ ሰብሳቢ ወ/ሮ ዙፋንን ጨምሮ ሌሎች ምሁራን እና በኦስሎ እና አካባቢው ነዋሪ የሆኑ ኢትዮጵያውያን ተገኝተዋል።
የውይይቱ መርሃ ግብር ከመጀመሩ በፊት የመርሃ ግብሩ መሪ የስብሰባው አላማዎች ማህበራዊ እሴት ምንነትን ማሳወቅ፣እንደ ሕብረተሰብ እና እንደ አገር ያለንበትን ደረጃ ማጤን እና ለመፍትሄው ያለንን ድርሻ መለየት መሆኑ ገልጦ ማሕበራዊ እሴት በሰዎች መካከል እና በማህበራዊ ተቋማት መካከል እና ግለሰቦችም ከእነኝህ ማህበራዊ ተቋማት ጋር ያላቸው ግንኙነት ሁሉ መሆኑን እና የእዚህ ሁሉ ትልቁ ዋጋመተማመንመሆኑን አብራርቷል።
በመቀጠልም  በማኅበራዊ እሴት ዙርያ ፅሁፎችን ይዘው የቀረቡትን ሶስት እንግዶች ወደ መድረኩ ጋብዟል።
ፅሁፎች ይዘው የቀረቡት:
1ኛ/ ወ/ሮ ዙፋን አማረ የኢትዮጵያ ማኅበረሰብ ሊቀመንበር፣
2ኛ/ አቶ እንግዳሸት ታደሰ የኖርወጅኛ አማርኛ መዝገበ ቃላት መፅሐፍ አዘጋጅ እና
3ኛ/ አቶ አጥናፉ ወ/ማርያም በኖርዌይ አገር ከ24 አመታት በላይ በመምህርነት ያገለገሉ እና አሁንም እያገለገሉ ያሉ ናቸው።
በመጀመርያ ፅሁፋቸውን ያቀረቡት ወ/ሮ ዙፋን ሲሆኑ የእርሳቸው ፅሁፍ በሚከተሉት ነጥቦች ላይ ያተኮረ ነበር።ይሄውም:
– ሀብት በእራሱ ሁለት አይነት መሆኑን እርሱም ሙት ሀብት ወይንም ፍሬ የማያፈራ እና ትርፍ የሌለው እና ሕይወት ያለው እና ፍሬ የሚያፈራ መሆኑን፣
– ሕይወት ያለው ወይንም ፍሬ የሚያፈራ ከሚባለው ውስጥ ማሕበራዊ እሴት አንዱ መሆኑን፣
– ማኅበራዊ እሴት ከሌላው የሚለየው የጋራ መሆኑ እንደሆነ፣

Deputy Chief of Ethiopian intelligence removed from office ESAT News (May 24, 2016)


Reports reaching ESAT from Addis Ababa say the second-in-command of the Ethiopian intelligence, Essayas Woldegiorgis has been removed from his post. The wife of Woldegiorgis, who is also an employee of the Ethiopian National Intelligence and Security Service, has also been fired.
Essayas Woldegiorgis is the central committee member of the ruling Tigray People’s Liberation Front. It is not clear if he still maintains his position in the party. He is now kept under watch by security forces, according to the sources.
Woldegiorgis is a veteran of the TPLF since its days as a guerilla group and was the head of the notorious “Bado Sidist,” a torture dungeon of the Front, where dissenters undergo unimaginable torture before they are executed.

ጥብቅ መረጃ የቴድሮስ አድሐኖም እጮኛ ቆንጂት !



የቴወድሮስ አድሐኖም ተወካይና ፖለቲካ ጉዳይ ሚኒስቴር ዲኤታ ናቸዉ እኚህ ግለሰብ በአሁኑ ወቅት የትግራይ ነጻ አዉጪ ቡድን ዉስጥ ቀንደኛ በመሆን ይንቀሳቀሳሉ ከብሔራዊ መረጃ እና የደህንነት ደንብ ክንፎች ጋር የጠበቀ ግንኙነት ሲኖራቸዉ አድራጊ ፈጣሪ በመሆን ግንባር ቀደሙን የደም ቡድንያራምዱታል ከታች በፎቶ የተቀመጡት ግለሰብ አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴ ይባላሉ የፅ/ቤታቸዉ ዋና ሐላፊ ( chef duty cabinet ) 
ችፍ ዲፒዉቲ ካቢኔዉ ደግሞ አምባሳደር በረደድ አንሙት የሚባሉ ግለሰብ ናቸዉ::

Tuesday, May 24, 2016

የኢትዮጵያ ወታደሮች ደቡብ ሱዳን መግባታቸው ተገለጸ ኢሳት (ግንቦት 16 ፥ 2008)


የኢትዮጵያ ወታደሮች ባለፈው ወር ከጋምቤላ ክልል ታፍነው የተወሰዱ ህጻናትን ለማስለቀቅ በድጋሚ ወደ ደቡብ ሱዳን መግባታቸው ተገለጸ።
ወታደሮች በሃገሪቱ የቦማ ግዛት ቢደርሱም የግዛቲቱ ባለስልጣናት ወታደሮቹ የቦማ ግዛትን አልፈው ለመሄድ በሚያደርጉት እንቅስቃሴ ላይ ፈቃድ ሳይሰጣቸው መቀረቱን ሱዳን ትሪቢዩን ጋዜጣ የግዛቲቱን ባለስልጣናት ዋቢ በማድረግ ማክሰኞ ዘግቧል።
የደቡብ ሱዳን መንግስት ተወካዮች ከሙርሌ ጎሳ ታጣቂዎች ጋር ሲያካሄዱት በነበረው ድርድር ታፈነው ከተወሰዱት ከ100 በላይ ህጻናት መካከል ከግማሽ በታች የሚሆኑት ብቻ መለቀቃቸው ይታወሳል።

ሰበር ዜና.. ጌታቸዉ አሰፋ ስብሰባ አቋርጦ ወጣ..

Getachew Assefaበትናንትናዉ እለት የወያኔ ተላላኪ ከሆኑት እና ከብሔራዊ መረጃ ጋር የጠበቀ ግንኙነት ካላቸዉ ግለሰቦች መካከል አምባሳደር ቀጸላ ከብሀራዊ መረጃዉ ሐላፊ ከጌታቸዉ አሰፋ ጋር አርበኞች ግንቦት 7 በአርባ ምንጭ ላይ የወሰደዉን እርምጃ ተንተርሶ ዉይይት በሚያደርጉበት ወቅት በተመሳሳዩ በደቡብ ኢትዮጵያ ኮንሶ አካባቢ በትግራይ ነጻ አዉጪ ቡድን መከላከያ ሰራዊት ላይ ጥቃት ተፈስሞ ከ 55 በላይ የሚጠጉ የፖለቲካ እስረኞች ማምለጣቸዉ 19 የወያኔ ታጣቂዎች መገደላቸዉና ቁስለኛ መሆናቸዉን የሚያበስር ዜና በስብሰባዉ ላይ የደረሰዉ ጌታቸዉ አሰፋ በአፋጣኝ ስብሰባዉን አቋርጦ መዉጣቱን ታማኝ ምንጮች ገልጸዋል።
አርበኞች ግንቦት 7 በፓርላማ ዉስጥ ሳይቀር መነጋገሪያ እርእስ መሆኑን የገለጹት ምንጮቻችን አክለዉ የወልቃይት ጠገዴ ጉዳይ የፈጠረዉ ፖለቲካዊና ህዝባዊ ጫና እንዳለ ሆኖ በጎንደር አርማጭሆ ሁመራ እና በትግራይ ጎንደር አዋሳኝ በኡማህጅር አካባቢ ድንገተኛና አደገኛ ጥቃቶች መሰንዘራቸዉን እንዲሁም በ24 እና በ25ኛ ክፍለጦር ተዉጣጪ የጸረ ሽብር ሐይል ላይ በተደረገ ሽምቅ ዉጊያ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱን መረጃዎች ጠቁመዋል።

ዜና – በልዑል አለሜ

በተለምዶ አሜሪካ ግቢ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ ለዘመናት የኖሩ ዜጎች “መጠለያ አልባ” ሊሆኑ እንደሚችሉ ተናገሩ


ግንቦት ፲፮ (አሥራ ስድስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በአዲስ አበባ ቤት የማፍረስ እርምጃው መቀጠሉትን ተከትሎ፣ ከትናንት ጀምሮ መርካቶ የሚገኘውና በተለምዶ አሜሪካ ግቢ በሚባለው አካባቢ እና አጎራባች ቀበሌዎች የሚገኙ ቤቶች እየፈረሱ ነው። ይህን ተከትሎ በአካባቢው ለረጅም ጊዜ የኖሩ ዜጎች ተለዋጭ መጠለያ ባለማግኘታቸው ማደሪያቸውን በቤተክርስቲያን ፣ በመስጊድ ወይም በጎዳናዎች ላይ ሊያደርጉ ይችላሉ ሲሉ አንዳንድ ነዋሪዎች ተናግረዋል።
ወኪላችን በስፍራው ተገኝቶ ያነጋገራቸው ሰዎች ፣ በአካባቢው አዳዲስ ህንጻዎች መሰራታቸው ተገቢ ቢሆንም፣ ደሃውን እያስለቀሱና ቤት አልባ እያደረጉ መሆን አልነበረበትም ይላሉ።
ነዋሪዎች እንደሚሉት፣ ለተነሽዎች 25 ካሬ ቦታ እንሰጣለን በሚል ከሶስት አመታት በፊት ቃል የተገባ ቢሆንም፣ ምንም አይነት ተለዋጭ ቤትና ቦታ ሳይሰጥ አብዛኞቹ እቃዎቻቸውን ሳየወጡ ልቀቁ በመባላቸው ችግር ላይ ወድቀዋል። ከዚህም አልፎ ደምብ አስከባሪዎችና ፖሊሶች ህዝቡን በዱላ እንደሚማቱ ነዋሪዎች ገልጸው፣ ድርጊቱ አገር እመራለሁ ከሚል መንግስት እንደማይጠበቅ ገልጸዋል።
ቤታቸውን ያላፈረሱ ሰዎች ንግድ ፈቃዳቸውን መቀማታቸውን የሚገልጹት ነዋሪዎች፣ በአገሪቱ አንድ አመጽ ቢነሳ በበዳዮች እና በተበዳዮች መካከል የሚኖረው ግጭት የከፋ እንደሚሆን ያስጠነቀቅቃሉ።

ሰበር ዜና የብሄራዊ መረጃ እና ደህንነት አገልግሎት ምክትል ዋና ሃላፊ አቶ ኢሳይያስ ወልደ ጊዮርጊስ ከስልጣናቸው ተባረሩ።


ባሌቤታቸውም ከስራቸው የተነሱ ሲሆን፡ ሁለቱም በጸጥታ ሃይሎች ክትትል ውስጥ ይገኛሉ።በአቶ ኢሳይያስ ምትክ በደርግ ዘመን የደርግ ደህንነት የነበሩት ሃደራ አበራ ተክተዋቸዋል።ለቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ባለቤት ወ/ሮ አዜብ መስፍን ቅርብ የነበሩት አቶ ኢሳይያስ ወልደጊዮርጊስ መባረራቸውን ተከትሎ በሌሎች ሃላፊዎችም ሆነ ሰራተኞች ላይ ስለተወሰደ ርምጃ የታወቀ ነገር የለም።ው/ሮ አዜብ መስፍን ግን የአቶ ኢሳይያስን ስንብት ተከትሎ ባለፈው ቅዳሜ አሜሪካ ገብተዋል፡ ዋሺንግተን ዳላስ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ ካሜራ ዕይታ ውስጥ የገቡት ወ/ሮ አዜብ መስፍን ከአንድ ልጃቸው ጋር ሰለመጡብት ምክንያት በውል የታወቀ ነገር የለም።

የአርበኞች ግንቦት 7 ከፍተኛ አመራር ዶ/ር ታደሰ ብሩ ከአሜሪካን ሀገር የተለያዩ ሴነተሮችና ባለስልጣናት ጋር በወቅታዊ የኢትዮጵያ ጉዳዮች ላይ ውይይት አደረጉ።



ዶ/ር ታደሰ ብሩ ለአጭር ጊዜ ጉብኝት አሜሪካን ሀገር የሚገኙ ሲሆን፤ በቆይታቸው ወቅት በኢትዮጵያ የሰባዊ መብት፣ ዴሞክራሲና መልካም አስተዳደር ዙሪያዎች ከአሜሪካን ኮንግረስማን ተወካዮች ጋር ውይይት አድርገዋል። በተለይም ከከሎራዶው ኮንግረስማን ማይክ ኮፍማን ጋር በወቅታዊ እና ዘላቂ መፍትሄዎች ላይ አመርቂ ውይይት ማድረጋቸው ተገልጾል።
ኮንግረስማን ኮፍማን ዶ/ር ታደሰን ስለ ኤርትራ ቆይታቸው ምን እንደሚመስል ጠይቀዋቸው፡- ዶ/ር ታደሰም ሲመልሱ፡- በህወሃት መንግስት የሚደረገው ህዝብን የማጣላት፣ በኢትዮጵያና ኤርትራ ህዝበ መካከል በጠላትነት እንዲተያዩ የሚያደርገው ዘመቻ የተሳሳተ መሆኑን ገልጸው አርበኞች ግንቦት 7 ዘላቂ ወዳጅነትን እየጠናከረ እንደሚገኝ እና የሁለቱ ህዝብ ጠላት TPLF እንጂ ሌላ መሰረታዊ ችግርች እንደሌሉ እና ለኤርትራ ህዝብ ያላቸውን አድንቆት በመግለጽ አብሮ መስራት እንደሚቻል ያላቸውን እምነት ገልጸውላቸዋል። አሜሪካ በኢትዮጵያ የምትከተለውን የውጪ ፖሊሲዋን እንደገና እንድትመረምረውም አሳስበዋል። አያይዘውም ኮንግረስማን ማይክ ኮፍማንና ሌሎች ሴነተሮች በቅርቡ በሜሪላንዱ ሴነተር ካርደን ቤንጃሚን ተረቆ የቀረበውን Resolution 432 በርካታ ሴነተሮች የፈረሙበትን የኢትዮጵያ ሰበአዊ መብትና ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ድጋፋቸውን ይሰጡ ዘንድ ኮንገርሰማኑን ጠይቀዋል።
በመጨረሻም ኮንግረስማን ማይክ ድርጅቱ በሁለቱ ሀገራት ህዝብ መካከል እየፈጠረ ያለውን የሰላም ድልድይ እና የማቀረረብ ሂደት አድንቀው፤ የኢትዮጵያን ወቅታዊ ጉዳዮችም እንደሚከታተሉ ገልጸውላቸዋል።
Abbay media

*በኮንሶ የመብት ጥያቄ በማንሳታቸው ከወር በፊት በእስር ቤት ከታጎሩ እስረኞች መካከል 59 የሚሆኑት እስር ቤት ሰብረው አምልጠዋል። ሰበራውን ያቀነባበሩት "ትግላችን ይቀጥላል!" ይላሉ



*በሐሮማያ ዩኒቨርስቲ ትምህርት ሙሉ ለሙሉ ተቋርጧል፣ ከድብደባ እና ጥይት የተረፉ ተማሪዎች ወደየቤታቸው ሄደዋል። ታደሠ የተባለ የሀይርድሮሎሊክ ኢንጂነሪንግ ተማሪ መገደሉ እየተነገረ ነው።
ኅዳር 1 የጀመረው የኦሮሚያ ሕዝባዊ ንቅናቄ ጋብ ያለ ሲመስል አመጹን አንቀሳቅሰዋል፣ ተሳትፈዋል የተባሉ ተማሪዎችን የመንግስት ደህንነትና ፖሊሶች እያፈኑ መውሰዳቸው በዩኒቨርስቲው ዳግም አመጽ እንዲነሳ ማድረጉን ተማሪዎች ይገልጻሉ።
*77 ቢሊየን ብር የፈሰሰበትን 10 የስኳር ፕርሮጀክቶች ግንባታ ኮንትራት ወስዶ ከግንባታ ማጠናቀቅያ ጊዜው አልፎ 3 ዓመታት የተቆጠሩበት ብረታ ብረት እና ኢንጂሪንግ ኮርፖሬሽን ሜቴክ ዋና ዳይሬክተር ሜጀር ጀነራል ክንፉ ዳኘው "በግሌ አስተያየት፣ ስኳር ኮርፖሬሽን ውድቀት 
አለው ብዬ አላምንም፡፡ ስኳር ኮርፖሬሽን የወደቀበት ምክንያት በእንቶኔ ነው በእከሌ ነው ቢባልም፣ አይገባኝም፡" ሲሉ የተፈጠረውን ቀውስ አጣጥለዋል።
ተጨማሪ ፕሮግራሞች አሉን ኢሳትን አድምጡ!