Tuesday, May 17, 2016

አርበኞች ግንቦት 7 ከፍተኛ ቁጥር ያላቸውን ምልምል አርበኛ ታጋዮችን ሰሞኑን አሰልጥኖ አስመረቀ ፡፡



| የተመረቁት እነዚህ አርበኛ ታጋዮች ለወራት የወታደራዊ የፖለቲካና ሌሎች ስልጠናዎችን የወሰዱ ሲሆን የተሰጣቸውን ስልጠና በብቃት መወጣታቸው ተገልፇል ፡፡ ተመራቂዎቹ እንደገለፁት የተሰጣቸው ስልተና እጅግ በጣም ጥሩ የሚባል ሲሆን የህወሃትን አምባገንናዊ ስርአትን ገርስሶ ለመጣል የመጨረሻ አማራጭ የሆነውን የትጥቅ ትግልን ከግብ ለማድረስ የተሰጣቸው ወታደራዊ ትምህርትና የተግባር እንቅስቃሴዎች ከበቂ በላይ እንደነበር ገልፀዋል፡፡ ያገኙት የፖለቲካ ትምህርትም የእውቀት አድማሳቸውን ያሰፋ እንደነበርና በተጨማሪም የወሰዱትን ወታደራዊ ስልጠና ተግባር ላ ለማዋል አይነተኛ መሳሪያ እንደሆነ አስረድተው ሌሎች ስልጠናዎችም እጅግ በጣም ጥሩና ለሚፈፅሙት ተልዕኮ ወሳኝ እንደነበሩ አክለው ገልፀዋል ፡፡
አርበኞች ግንቦት 7 ወታደራዊ አቅሙ እየጎለበተና አረያደገ የሚገኝ ሲሆን የቆመለትን አላማ ማለትም የኢትዮጵያ አንድነትና ዴሞክራሲ የመገንባት ሂደት እንቅፋት የሆነውን የህውሃት ስርአትን ለማስወገድ የጀመረውን ጉዞ በድል ለማጠናቀቅ ከተለያየ የሃገራቸህን ክፍል የተሰባሰቡት እነዚህ ተመራቂዎች በተለያየ ፆታና የዕድሜ ክልል ላይ የሚገኙ ሲሆኑ የህወሃትን ስርዓት ለማስወገድ በሰላማዊ መንገድ ይታገሉ የነበሩ ሰላማዊ ታጋዮችም ይገኙበታል፡፡http://www.patriotg7.org/…/uploads/2016/05/AG7-radio-17-05-…

No comments:

Post a Comment