Friday, March 27, 2015

Discover Ethiopia: The 14th Century Town, Birth Place of Emperor Menelik II

አርበኞች ግንቦት 7… እየመጡ ነው! አርበኞች ግንቦት 7… አዲስ አበባ ድረስ ሊመጡልህ አይደለም ወይ… ==================================================== ሰሞኑን ወያኔ እየደለቀው የሚገኘው “የጦርነት ክተት አዋጅ” አታሞ ለጆሯችን አዲስ አይደለም፡፡ የተለመደ ከተራና ትርጉምየለሽ የፖለቲካዊና ወታደራዊ ፕሮፖጋንዳ ያላለፈ ፍርሃት ከወለደው ጭንቀት የመነጨ ቅዠት /Nightmare/ የእንቅልፍ ዓለም እንቅስቃሴ /Somnambulism/ ነው፡፡ ህ.ወ.ሓ.ት ጠብመንጃና ጥይት እንጂ የመዋጋት ስነ-ልቦና ፈፅሞ በውስጡ የሌለውን መከላከያ ሰራዊቱን ቢያንስ፣ ቢያንስ በየስድት ወሩ ወደ ኤርትራና ሱዳን ድንበሮች የስጠጋል፣ መልሶ ያሸሻል ያስጠጋል መልሶ ያሸሻል፡፡ በኦጋዴን በኩልም ከኦብነግና አልሸባብ ጋር በተያያዘ እንዲሁ ነው፡፡ አራቱን የሂሳብ ስሌቶች እንኳን ጠንቅቀው የማያውቁት የወታደራዊ ሳይንስ ሽፍታ “ጨዋ” የህ.ወ.ሓ.ት ጀነራሎች ተግባራቸው ሁሉ ውሃ ቅዳ ውሃ መልስ ከሆነ ከራርሟል፡፡ ሟች በሌለበት ገዳይ መሆናቸው እና የሚገባላቸው አያገኙም እንጂ ወጣቶችን በሀገር መከላከያ ስም ለስልጣናቸው እድሜ ማራዘሚያ ለመመልመል ማስታወቂያ ማውጣታቸውም ቢሆን ከዚህ በፊት እየተደጋገመ ያሰለቸን ጉዳይ ነው፡፡ ወያኔዎች እንደ ከዚህ ቀደሙ ዛሬም ወደፊትም አይዋጉም፡፡ በ1991 ዓ.ምና በ92 ዓ.ም የተዋጋው የኢትዮጵያ ህዝብ ነው፡፡ በትንሹ ከ100 ሺህ በላይ የድሀ ልጆች በከንቱ ረግፈው ቀርተዋል፡፡ ድሉ ግን የወያኔዎች ብቻ ነበር፡፡ አሁንም ቢሆን የወያኔዎ ዕቅድና ፍላጎት ከዚህ የተለየ አይደለም፡፡ ሽማግሌው ስብሃት ነጋ ለአሜሪካ ድምፅ ሬድዮ የትግርኛ ፕሮግራም “የኤርትራ ጉዳይ ያስተዳደር እንጂ የቅኝ ግዛት አይደልም…” በማለት ከ40 ዓመታት በኋላ ድርጅታቸው ህ.ወ.ሓ.ት አቋሙን መለወጡን ማስታወቃቸው፤ በተጨማሪም ወያኔ-ኢህአዴግ ለምርጫ ቅስቀሳ በየጊዜው የሚለቃቸው ዶክመንተሪዎች የአድዋን ድልና ሌሎችን የህዝቡን ስነ-ልቦና ማስተሳሰሪያ ጠንካራ የታሪክ ክሮች እየመዘዘ ማሳየቱ ከዛሬ 14 እና 15 ዓመታት በፊት እንደሆነው ህዝቡን ለጦርነት በማነሳሳት የድሃ ልጅ የሆኑ ወጣቶችን ደመራ በማድረግ ዳር ሆነው ለመሞቅ ነው፡፡ የሰሞኑ ፕሮፖጋንዳቸው ንፋስ ትክክለኛ አቅጣጫ ይሄ ነው፡፡ ነገር ግን በጠብመንጃ አስገድደው አፉን በማስከፈት የግፍ ገፈት እየጋቱት የሚገኘውን መከረኛ የኢትዮጵያ ህዝብ ልክ እንደበፊቱ ዛሬም በቀላሉ ማታለል እንደማይቻል ልቦናቸው ጠንቅቆ ያውቀዋል፡፡ ወያኔ ፈለገም አልፈለገም ጦርነቱ አይቀሬ ነው፡፡ ህዝቡ ራሱን መጠየቅና መልስ መስጠት ያለበት ቁምነገር ቢኖር ወያኔ ጦርነት የሚገጥመው ከነማን ጋር ነው? የሚለውን ነው፡፡ ወያኔ በጥሩንባ እንደሚያስለፍፈው ጦርነቱ የምር ከኤርትራ ጋር አይደለም፡፡ ኤርትራ ውስጥና በኤርትራ ዙሪያ በሚገኙ ጀምበር እቶን እሳቷን ከምታራግፍባቸው ነዲድ የሚተፉ በረሃዎች ውስጥ ከመሸጉ የነጻነት ፋኖዎች የምንጊዜም ጀግና የኢትዮጵያ ልጆች ጋር እንጂ፡፡ እነዚህ የነፃነት አርበኛ ውድ የኢትዮጵያ ወጣቶች ትምህርታቸውን፣ ስራቸውን፣ ስልጣናቸውን፣ ትዳራቸውን፣ አንዳንዶቹ ልጆቻቸውን… ባጠቃላይ የተደላደለ ኑሯቸውን ትተው ከአገርቤት፣ ከአውሮፓና ከአሜሪካ ወደ በረሃ የወረዱት ለኢትዮጵያ ህዝብ ነፃነት ሲሉ ብቻ ነው፡፡ ለኢትዮጵያ ህዝብ አንድነት፣ ነፃነት፣ ፍትህና ዴሞክራሲ ሲባል ክቡር ህይወታቸውን ዋጋ ለመክፈል ተዘጋጅተው በሃሩር እየነደዱ ቁራሽ ቂጣ አሸዋና ጭቃ በተቀላቀለበት ድፍርስ ውሃ አወራርደው ከዘንዶ፣ እባብና ጊንጥ ጋር እየታገሉ ውለው የሚያድሩ ናቸው፡፡ ዛሬ የዋጣቸውን ጥቅጥቅ ጨለማ ሳይሆን ከተራራው ወዲያ ከአድማስ ማዶ የምትታየውን፣ የነፃነት ጎህ የቀደደባትን፣ የነገዋን ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ አሻግረው እዕምሯቸው ውስጥ በሚገኙ ትልልቅ ዓይኖቻቸው እየተመለከቱ መንፈሳቸው በፅናት የተሞላና ነብሳቸው በፍስሃ የተጥለቀለቀች ታሪክ ለመስራት የሚሻሙ ሀዋሪያዎች ናቸው፡፡ ከግማሽ ምዕተ ዓመታት በላይ ሲንከባለል የመጣ የህዝብ የነፃነት ጥያቄ ከትከሻቸው ላይ ያረፈ ለህዝብ ሲባል ልክ አንደ ሰማዕቱ አቡነ ጴጥሮስ ሞትን ገጥመው ያሸነፉ የዚህ ትውልድ አካል ናቸው፡፡ ስልጣን ፈላጊነት፣ ማናቸውም ቁሳዊ ፍላጎቶችና ልክ እንደ ደደቢቱ ህ.ወ.ሓ.ት ከህዝብ የተደበቀ ስውር ዓላማ ፈፅሞ የሌላቸው አልፋና ኦሜጋ የሆነ ታሪክ በደማቸው ለመፃፍ ከሁሉም የኢትዮጵያ አካባቢዎች ተፈጥረው በአንድ ዓላማ ዙሪያ በመሰባሰብ በአንድነት የቆሙ ንፁህና ጭቁን የኢትዮጵያ ልጆች ናቸው፡፡ ይሄንን እውነት የኤርትራ በረሃ ተራሮች፣ በአፅም ስብርባሪ የዳበረው አፈር፣ ሳር ቅጠሉ ጭምር አፍ አውጥቶ ይናገራል፡፡ ስልጣንና ቁሳዊ ፍላጎት ያለው ኢትዮጵያ ውስጥ እንጂ በኤርትራ በረሃዎች ውስጥ አይደለም፡፡ ስልጣንና ገንዘብ ለማግኘት የሚያስፈልገው ህሊናን ሸጦ ከወያኔ መጠጋት እንጂ በረሃ ወርዶ አፈር ላይ መተኛት አይደለም፡፡ ይህ ከበረዶ የነጣ ሀቅ ደግሞ ነገ በተግባር ይገለፃል፡፡ ስለሆነም የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ! ከአንተ ተፈጥረው፣ ላንተ ነፃነት ብለው፣ አንተ የጉልበታቸውና ኃይላቸው ምንጭ ስለሆንክ በአንተ ተመክተው፣ ለአንተ ለመሞት ቆርጠው በረሃ የወረዱ ጀግኖች ልጆችህን ነው ህ.ወ.ሓ.ት ከጎኔ ተሰልፈህ ውጋቸው እያለህ የሚገኘው፡፡ ወያኔ የሚያደርገው ጦርነት አንተ ነፃ ሳትወጣ ወደፊትም በባርነት ቀንበር አንገትህን ታንቀህ በዘረኛ አገዛዝ ስር እድሜ ልክህን እየማቀቅህ እንድትኖር ሲባል የሚደረግ ነው፡፡ ይህ ነው እውነታው እወቀው… ወያኔ በኤርትራ በረሃዎች ውስጥ የሚንቀሳቀሱ ብረት ያነሱ የነፃነት ኃይሎችን ከኤርትራ ጋር በሚደረግ ጦርነት ስም ለመደፍጠጥ የጦርነት ፕሮፖጋንዳ ወጀብ ማስነሳቱ ያለህዝብ ድጋፍ በወታደርና ጦር መሳሪያ ብዛት አንድ ስንዝር እንደማይራመድ ጠንቅቆ ስለሚያውቀው ነው፡፡ አይጥ ለሞቷ የድመት አፍንጫ ታሸታለች፡፡ ምናልባት ሁሉም ህዝብ ጠለቅ ብሎ ላያውቅ ይችላል አላጥሽ፣ ማይካድራ፣ አዲ ጎሹ፣ በረከት፣ ሉግዲ፣…. ላይ በሚመሩት ሰራዊት ላይ የነፃነት አርበኞች የፈፀሙትን የህ.ወ.ሓ.ት ጀነራሎች እነ ሳሞራ የኑስና ሳዕረ መኮንን አሳምረው ያውቁታል፡፡ በእርግጥ የእነሱ ሰራዊት ይሁን እንጂ ታጭዶ አስከሬኑ መሬት ላይ የተነሰነሰው ጭቁን የድሃ ልጅ ነው፤ ያውም በዘር ወንፊት ተነፍቶ በእሱ ደም ምኒልክ ቤተ መንግስት ለመሰንበት እሳት ውስጥ የተማገደ፡፡ በሁለትና ሦስት ታጋይ እንደበግ የሚነዳ ሰራዊት፤ ገና የጥይት ድምፅ ሲሰማ ከተኛበት ተነስቶ በውስጥ ሱሪ ብቻ ከካምፕ ወጥቶ ወደ ከተማ እግሬን አውጭኝ የሚል፤ ከሆነ ቦታ ተነስተው ታጋዮች ወደ እሱ እየገሰገሱ እንደሆነ ሲሰማ ገና ሳይደርሱበት በርቀት ከባዶ ሜዳ ተኩስ ከፍቶ ጥይቱን በመጨረስ ተኩላ እንዳየ የበግ መንጋ በርግጎ የትሙን በመበታተን የሚጠፋ… መከላከያ ሠራዊት እንደሚመሩ የህወሓት ጀነራሎች በሚገባ ያውቃሉ፡፡ ሰራዊቱ በጠቅላላ ከጓድ ጀምሮ እስከ ዕዝ ድረስ ተመሳሳይ ቋንቋ በሚናገሩ የህ.ወ.ሓ.ት ታማኝ ሰዎች ተጠርንፎ ሳይወድ በግድ በጉልበት የተያዘ እንጂ እሺ ብሎ በፍላጎቱ እንደማይዋጋላቸውም ጭምር የህ.ወ.ሓ.ት ጀነራሎች በጠቅላላ ያውቃሉ፡፡ አዎ በኢሳት ቴሌቪዥን በምሬትና በወኔ ሲናገሩ የሚታዩት የነፃነት ታጋዮች እንደ አኬልዳማና ጃሃዳዊ ሀረካት ለፕሮፖጋንዳ ሲባል ብቻ የሚተውኑ የቴአትር ገፀ-ባህሪያት አይደሉም በገሃዱ ዓለም በኤርትራ በረሃዎች ውስጥ በእውን የሚገኙ እንጂ፡፡ ምሬትና ቁጭታቸው እንዲሁም ወያኔን ለመደምሰስ ያላቸው ወኔ በቴሌቪዥን ስክሪን ከሚታየው በእጅጉ የላቀ ነው፡፡ ትግርኛ ቋንቋ ተናጋሪዎችን እየመረጥክ በሰላም ወረዳ በማስቀረት ሌሎችን አንተ የእኔ ወገን አይደሉም የምትላቸውን ጭቁን የኢትዮጵያ ልጆች የሆኑ የመከላከያ ሰራዊት አባላትን ወደ ጦርነት የምትልከው “መንግስት” ወያኔ ሆይ! ለምን ኤርትራ ድረስ በመዝመት መንገድ ትመታለህ አርበኞች ግንቦት 7… አዲስ አበባ ድረስ ሊመጡልህ አይደለም ወይ…Deginetu Zewdu Abebaw Netsanet Beqalu's photo. Netsanet Beqalu's photo. Netsanet Beqalu's photo. Unlike · Comment · Share

አርበኞች ግንቦት 7… እየመጡ ነው! አርበኞች ግንቦት 7… አዲስ አበባ ድረስ ሊመጡልህ አይደለም ወይ…
====================================================
ሰሞኑን ወያኔ እየደለቀው የሚገኘው “የጦርነት ክተት አዋጅ” አታሞ ለጆሯችን አዲስ አይደለም፡፡ የተለመደ ከተራና ትርጉምየለሽ የፖለቲካዊና ወታደራዊ ፕሮፖጋንዳ ያላለፈ ፍርሃት ከወለደው ጭንቀት የመነጨ ቅዠት /Nightmare/ የእንቅልፍ ዓለም እንቅስቃሴ /Somnambulism/ ነው፡፡ ህ.ወ.ሓ.ት ጠብመንጃና ጥይት እንጂ የመዋጋት ስነ-ልቦና ፈፅሞ በውስጡ የሌለውን መከላከያ ሰራዊቱን ቢያንስ፣ ቢያንስ በየስድት ወሩ ወደ ኤርትራና ሱዳን ድንበሮች የስጠጋል፣ መልሶ ያሸሻል ያስጠጋል መልሶ ያሸሻል፡፡ በኦጋዴን በኩልም ከኦብነግና አልሸባብ ጋር በተያያዘ እንዲሁ ነው፡፡ አራቱን የሂሳብ ስሌቶች እንኳን ጠንቅቀው የማያውቁት የወታደራዊ ሳይንስ ሽፍታ “ጨዋ” የህ.ወ.ሓ.ት ጀነራሎች ተግባራቸው ሁሉ ውሃ ቅዳ ውሃ መልስ ከሆነ ከራርሟል፡፡ ሟች በሌለበት ገዳይ መሆናቸው እና የሚገባላቸው አያገኙም እንጂ ወጣቶችን በሀገር መከላከያ ስም ለስልጣናቸው እድሜ ማራዘሚያ ለመመልመል ማስታወቂያ ማውጣታቸውም ቢሆን ከዚህ በፊት እየተደጋገመ ያሰለቸን ጉዳይ ነው፡፡

Wednesday, March 25, 2015

/ ጀነራል ለገሰ ተፈራ / የመጨረሻ ክፍል

/ ጀነራል ለገሰ ተፈራ / የመጨረሻ ክፍል
ጀነራል ለገሰና ጀነራል አሸናፊ ከግዳጅ መጥተው ለምሳ ሲዘጋጁ ከኮማንድ ፖስት ትእዛዝ መጣ። “......በጀነራል አብዱላሂ የሱፍ የሚመራ ከፍተኛ የሆነ ጦር በባሌ በኩል ጥቃት ከፍቷልና በፍጥነት ድጋፍ እንድትሰጡ.....” የሚል። ሁለቱም ጀነራሎች ምግብ ሳይበሉ ወደ አውሮፕላናቸው ሮጡ። የካምቤራው ( ቦምብ ጣይ ) አብራሪ መስፍን ኃይሌ ቀድሞ ተነሳ። ለገሰ እና አሸናፊ ተከታትለው ተነስተው ቦም ጣዩን አጀቡት። ቦታው ላይ እንደደረሱ ለገስ ለመስፍን ኃይሌ የጠላትን አሰላለፍ እና አቀማመጥ ለመንገር ዝቅ ብሎ መብረር ጀመረ። ሶማሌዎችም ያላቸውን መሳሪያ ሁሉ ተኮሱ። .....የለገሰም አውሮፕላን ተመታች።.... ለገሰም ጠላት እጅ ገባ። ሶማሌዎች ለመጀመሪያ ጊዜ የኢትዮጵያን አውሮፕላን መትተው ጣሉ። ሰፈራቸው ፌሽታ ሆነ። ፈነጠዙ። ኢትዮጵያን የተቆጣጠሩ መሰላቸው።
ጀግናው ለገሰ በሱማሌዎች ከተያዘ በኋላ በእስር ቤት ለአስራ አንድ አመታት ያህል ቆይቶ በ1981 ተፈታ። ለገሰ በእስር ቤት ሳለ ከፍተኛ ስቃይ ስለደረሰበት ከእስር ተፈትቶ ወደ አዲስ አበባ በመጣበት ጊዜ ሰውነቱ አልቆ ከሞት የተነሳ አጽም ይመስል ነበር፡፡ ሊቀመንበር መንግሥቱ ጄኔራል ለገሠን በከፍተኛ ወታደራዊ ስነ-ስርዓት ከተቀበሉት በኋላ የሀገሪቱ የመጨረሻ ደረጃ ኒሻን የሆነውን “የህብረተሰብአዊት ኢትዮጵያ ጀግና ሜዳይ” ሸልመውታል፡፡ የአሁኑም የኩባው ፕሬዝዳንት ራውል ካስትሮ ለገሰን ከነቤተሰቡ ጋብዘውታል።
ክብር ለጀግኖቻችን !
አመሰግናለሁ......

የአዲስ አበባ አስተዳደር ለመሬት ዋጋ ንረት መንስዔ በስፋት አለመቅረቡ ነው አለ - ሳተናው (Satenaw) -Latest Ethiopian News & Breaking News

የአዲስ አበባ አስተዳደር ለመሬት ዋጋ ንረት መንስዔ በስፋት አለመቅረቡ ነው አለ - ሳተናው (Satenaw) -Latest Ethiopian News & Breaking News

ለምወደው እና ለማከብረው ሕዝብ እውነትን የሚገልጽ ውሃን የሚተፋ እንጂ እሳትን የሚተፋ ብዕር የለኝም።

ለምወደው እና ለማከብረው ሕዝብ እውነትን የሚገልጽ ውሃን የሚተፋ እንጂ እሳትን የሚተፋ ብዕር የለኝም።

Tuesday, March 24, 2015

ይህ የወያኔ ጄኔራል የሚያለቅሰው የኢትዮጵያ ህዝብ ላይ እየደረሰ ባለው ሰቆቃ ቢሆን ይሻል ነበር

የወያኔ ጀኔራሎችና ባለስልጣናት ብርክ ላይ ናቸው የመቸረሻ ስብከታቸውም ኤርትራ ውስጥ ነፃነት ታጋይ ሚባል ይቅርና አንድም የሸፈተ ኢትዮጵያዊ ለም፡፡ ሻቢያ ብቻ ነው ያለው የሚል ወታደራዊ ስብሰባ ላይ ተተምዶ እደሰነበተና የየጦር ሰራዊትና ክፍሉንም እንዲዘጋጁ ተናግረዋል፡፡

የወያኔ ጀኔራሎችና ባለስልጣናት ብርክ ላይ ናቸው የመቸረሻ ስብከታቸውም ኤርትራ ውስጥ ነፃነት ታጋይ ሚባል ይቅርና አንድም የሸፈተ ኢትዮጵያዊ ለም፡፡ ሻቢያ ብቻ ነው ያለው የሚል ወታደራዊ ስብሰባ ላይ ተተምዶ እደሰነበተና የየጦር ሰራዊትና ክፍሉንም እንዲዘጋጁ ተናግረዋል፡፡
====================================================
የወያኔ ጀኔራሎች የተቃዋሚዎችን ሃይልና አቅም በመፍራት እና መከላከያ ሰራዊቱ ወደ ነፃነት ታጋይ ወገኖቻቸው ይቀላቀላሉ ብሎ በመፍራት እንዲሁም ቤቀኑ እየሄዱ ሚቀላቀሏቸውን ኢትዮጵያዊያን ሲቪሎችና ሲቪል ልብስ እየለበሱም እስሙሉ ትጥቃቸውም የሚቀላቀሏቸውን በማየት ለቀሪው ሰራዊት ግራ ማጋቢያ አለኝ የሚለውን ሃሳቡን በማሰራጨትና ስብሰባ መዓት በማብዛት ላይ ይገኛል፡፡
ወያኔ ጀኔራሎችና ባለስልጣናት ነባር ታጋዮች ሳይቀር ተርበትብተዋል በዚህም ምክንያት
"… ኤርትራ ውስጥ ምንም ኢትዮጵያዊ የነፃነት ታጋይ ሚባል የለም… ያለው ሻቢያ ብቻ ነው ሻቢያ ደግሞ የኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊያን ተላት ነው…

በአባይ አጠቃቀም ጉዳይ የመርኅ ስምምነት ተፈረመ የምሥራቅ ናይል ተፋሰስ አካል በሆኑት በኢትዮጵያ፣ በግብፅና በሱዳን መካከል የአባይ አጠቃቀምና የታላቁ ኅዳሴ ግድብ የመርኅ ስምምነት ዛሬ ተፈርሟል፡፡

በግብፁ ፕሬዚዳንት አብደልፋታህ ኤል-ሲሲ፣ የሱዳኑ ፕሬዚዳንት ኦማር ሃሰን አል-በሺርና የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሣለኝ - ኻርቱም፤ መጋቢት 14/2007 ዓ.ም /የፎቶ ምንጭ - አሾሺየትድ ፕሬስ - ከኢንተርኔት የተገኘ/
በግብፁ ፕሬዚዳንት አብደልፋታህ ኤል-ሲሲ፣ የሱዳኑ ፕሬዚዳንት ኦማር ሃሰን አል-በሺርና የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሣለኝ - ኻርቱም፤ መጋቢት 14/2007 ዓ.ም /የፎቶ ምንጭ - አሾሺየትድ ፕሬስ - ከኢንተርኔት የተገኘ/
ሰሎሞን አባተ


የኅዳሴ ግድብ ግንባታየኅዳሴ ግድብ ግንባታ
በአባይ አጠቃቀም ጉዳይ የመርኅ ስምምነት ተፈረመ
የምሥራቅ ናይል ተፋሰስ አካል በሆኑት በኢትዮጵያ፣ በግብፅና በሱዳን መካከል የአባይ አጠቃቀምና የታላቁ ኅዳሴ ግድብ የመርኅ ስምምነት ዛሬ ተፈርሟል፡፡
ስምምነቱ የተፈረመው በሦስቱ ሃገሮች መሪዎች፤ በሱዳኑ ፕሬዚዳንት ኦማር ሃሰን አል-በሺር፣ በግብፁ ፕሬዚዳንት አብደልፋታህ ኤል-ሲሲና በኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሣለኝ ኻርቱም ላይ በሱዳኑ ሪፐብሊካን ቤተመንግሥት ውስጥ በተከናወነ ሥነ-ሥርዓት ነው፡፡
የሰነዱን ይዘትና የስምምነቱን ምንነት አስመልክቶ የኢትዮጵያን የውኃ፣ ኢነርጂና የመስኖ ሚኒስትር አቶ አለማየሁ ተገኑ ለቪኦኤ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
አባይአባይ
ሚኒስትሩ በዚሁ ለቪኦኤ በሰጡት መግለጫቸው ላይ የአባይ አጠቃቀም በፍትሐዊነት ላይ ተመሥርቶ በሦስቱም ሃገሮች ላይ ብዙ ጉዳት የማያስከትል፤ በትብብር መርኅ ላይ የተመረኮዘ እንዲሆን የመርኅ ስምምነት ላይ መደረሱን እና አባይ ለሦስቱም ሃገሮች ሕዝቦች እኩል የሕይወትና የልማት ምንጭ መሆኑ በሠነዱ ላይ መስፈሩን አመልክተዋል፡፡
ከአቶ አለማየሁ ተገኑ ጋር የደረገውን ቃለምልልስ ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

ህዳሴም ሆነ ዉዳሴ ክህዝብ የሚደበቅ ምንም ነገር የለም! አርበኞች ግንቦት7 http://wp.me/p5TKit-1Dw9

ከሰሞኑ አገራችን ኢትዮጵያን በተለይም ብሄራዊ ጥቅሟንና ደህንነቷን በተመለከተ ሁለት አቢይ ዜናዎች የአገራቸን የኢትዮጵያንና የኢትዮጵያ ጉዳዮች በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የሚመለከታቸዉን አገሮች የአየር ሞገደች ተቆጣጥረዉት ነበር። ከእነዚህ ዜናዎች ዉስጥ አንዱና ዋነኛዉ ኢትዮጵያ፤ ሱዳንና ግብፅ የህዳሴዉን ግድብ አስመልክቶ ስምምነት ላይ ደረሱ የሚል ዜና …

የጄት ድብደባ ወይንስ የአውሮፕላን መከስከስ?

March 24, 2015
አበበ ገላው (ከፌስቡክ የተወሰደ)
ወያኔ ኤርትራ ውስጥ የሚገኝ አንድ የካናዳ የወርቅ ማእድን በአውሮፕላን መደብደቡን አፍቃሪ ወያኔ የሆኑ ድረ ገጾች “ወታደራዊ ምንጮችን” በመጥቀስ ዘግበዋል።
ይሁንና እንኳን ድብደባው የጥቃቱን ውጤት ያሳያል ተብሎ የተለቀቀውም ፎቶ የውሸት መሆኑ ተረጋግጧል። አውራንባ ታይምስ አስተማማኝ ምንጮችን ጠቅሶ ድብደባውን ማረጋገጡን የዘገበ ሲሆን ዘገባውም በፎቶ ማስረጃ የታጀበ ነው። ይሁንና ፎቶው የሚያሳው ኤርትራ ውስጥ የተኪያሄደውን የአየር ጥቃት ውጤት ሳይሆን ቢቢሲ በኦገስት 9 2013 አንድ የወያኔ አየር ሃይል የእቃ ማጓጓዣ አውሮፕላን ሞቃዲሹ ውስጥ ተከስክሶ ሲጋይ የሚያሳይ የፎቶ ማስረጃን ነው። ይህም ፎቶ የተነሳው በሮይተርስ ሲሆን በቢቢሲ ድረ ገጽ ላይ ከዜናው ጋር በክብር ታትሞ ይገኛል።

Friday, March 20, 2015

TPDM TV AMHARIC program 19 MAR 2015 PART TWO,ሊመለከቱ የሚገባው የወያኔ ሴራ በንግድ ድርጅቶች የሚደረገው ብዝበዛ,,,,,

Ethiopians rally in Geneva, SwitzerlandETHIOPIANS RALLY IN GENEVA, SWITZERLAND Ethiopians in Europe held massive rally against the TPLF regime in Ethiopia.

የወያኔ ባለስልጣናት ለሊቱን የጉምሩክ መጋዘኖችን ሲዘርፉ አደሩ::

ህጋዊና ፍትሃዊ ያልወነን ምርጫ እንቃወም!(በይበልጣል ጋሹ)

March 20, 2015
በይበልጣል ጋሹ
እውነት ነው “ምርጫ” ዲሞክራሲ በሰፈነበት አገር ከጦር መሳርያ በላይ ይፈራል፣ ይከበራልም። “ፍትሃዊ ምርጫ” ትልቅ ሰላማዊና ህጋዊ የትግል መስክ ነው። እርግጥ ነው ህዝብ መብቱ መከበሩን የሚያረጋግጥበት አይነተኛ ዜዴ“ህጋዊ ምርጫ” ነው። ህዝብ በምርጫ የሰጠው ድምጽ ሲከበርለት መብቱ ሊከበር እንደሚችል ማሳያ ምልክት ነው።Ethiopian election 2015
“ምርጫ” በሃገሪቱ የሚካሄደው አንድ ድርጅት ለስልጣን የሚበቃበትንና ስልጣን የሚያራዝምበትን አንድ ዲሞክራሲያዊ ምርጫ ብቻ እንዲካሄድ አድርጎ ስልጣን ለመጨበጥም ሆነ ስልጣን ለማስያዝ አይደለም። በዚያች ሃገር የሚካሄዱ ሁሉም ምርጫዎች ዲሞክራሲያዊ እንዲሆኑ ነው እንጂ። በአገሪቱ በስልጣን ላይ የሚቀመጠው አካል ሁልጊዜም በህዝብ ይሁንታ በሰላማዊና ህጋዊ ዲሞክራሲያዊ ምርጫ እንዲመነጭ ለማድረግ “ህጋዊ ምርጫ” ዋና መሳሪያ ነው። ይህን ህጋዊ ምርጫ ለማካሄድ ዲሞክራሲያዊ መንግሥት፣ ህጋዊ መንግሥት፣ ለሃገርና ለህዝብ የቆመ መንግሥት፣ነጻና ህጋዊ ምርጫ እንዲካሄድ ፍላጎት ያለው እና በምርጫ መሸነፍና ማሸነፍ እንዳለ የሚገነዘብ መንግሥት ያስፈልጋል። ይህ ካልሆነ ግን ምርጫ ፌዝ፣ ጭዋታና ቀልድ ነው የሚሆነው።
ነጻና ፍትሃዊ ምርጫ አምባገነናዊ፣ ዘረኛ፣ ጨቋኝና አረመኔ ሥርዓት በአለበት አገር ፈጽሞ የሚታሰብ አይደለም። ቢሞከርም ለይስሙላ ካልሆነ በስተቀር

በአውሮፓ ስዊዘርላድ ጄኔቭ ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ እየተካሄደ ነው:: ‪#‎Ethiopia‬ ‪#‎Geneva‬ ‪#‎Switzerland‬ ‪#‎HumanRights‬ ‪#‎MinilikSalsawi‬ ‪#‎EU‬ Minilik Salsawi - የወያኔ መንግስት በኢትዮጵያውያን ላይ እየፈጸመ ያለውን የሰብአዊ መብት ጥሰት እስር ግድያ እና ዘረፋ በመቃወም ለአለም አቀፉ ሕብረተሰብ እና መንግስታት ለማሰማት በዛረው እለት በአውሮፓ ስዊዝ መዲና ጄኔቭ ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ እየተደረገ መሆኑን ከስፍራው የተገኙ መረጃዎች ጠቁመዋል:: በሕወሃት ኢሕአዴግ ዘረኛ አገዛዝ በግፍ ወሕኒ ለተወረወሩ ወገኖቻችን በስዊዝ የመንግስታቱ ጽ/ቤት ደጃፍ ድምጻቸውን ለማሰማት የወጡ ኢትዮጵያውያን በርካታ ሲሆኑ በኢትዮጵያ ባንድራ ታጅበው የተለያዩ መፈክሮችን እና የታሳሪ እና ተጎጂ ወገኖቻችንን ምስል በመያዝ ድምጻቸውን በማሰማት ላይ ናቸው::

 የግቢዬ ዛፎች -ከተማ ዋቅጅራ - Zehabesha Amharic

 የግቢዬ ዛፎች -ከተማ ዋቅጅራ - Zehabesha Amharic

ተቀላቀሉን፤ ካልሆነም በያላችሁት ተደራጁ! March 20, 2015 pg7-logo

pg7-logo
ህወሓት በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ ስለሚያደርሰው ዘርፈ ብዙ በደል ብዙ የተነገረለትና የተፃፈበት ብቻ ሳይሆን እየኖርንበት ያለ ሀቅ ነው። የኢትዮጵያ ሕዝብም የሚደርስበትን ስቃይ መታገስ ወደማይችልበት ጫፍ መድረሱ በሰበብ አስባቡ በሚፈነዳዱ ተቃውሞዎች የሚታይ ሀቅ ሆኗል።

Tuesday, March 17, 2015

ወያኔና ሽብርተኛነት ፕ/ር መስፍን ወልደ-ማርያም http://www.goolgule.com/tplf-and-terrorism/ ወያኔነትና ሽብርተኛነት ትናንት ምን ዓይነት ግንኙነት ነበራቸው? ዛሬ ምን ዓይነት ግንኙነት አላቸው? ወደዚያ ከመሄዳችን በፊት የአሸባሪነት የተግባር መገለጫው ምንድን ነው? ብለን እንጠይቅ፤ አሸባሪነት፡-

Ethiopian journalist Temesgen Desalegn denied access to medical care in jail - CPJ

The health of Temesghen Desalegn has deteriorated in prison, but he has been denied medical care. (Awramba Times)

ግርማ ሠይፉ ማሩ girmaseifu32@yahoo.com; www.girmaseifu.blogspot.com ተከራካሪ “ፓርቲዎች” ኢህአዴግ፤ አቶ አሰመላሽ ገ/ስላሴ እና አቶ ሬድዋን ሁሴን (ዋና ተከራካሪ ማን እንደሆነ ባይነገርም ይታወቃል) አትፓ፤ አቶ አሰፋው ጌታቸው መድረክ፤ ዶር መረራ ጉዲና ሰማያዊ፤ አቶ ይልቃል ጌትነት እና አቶ ዮናታን ተሰፋዬ “አንድነት”፤ አቶ ትዕግሰቱ አወሉ - See more at: http://www.zehabesha.com/amharic/archives/39753#sthash.fxlRTrF3.dpufየምርጫ ክርክር አንድ፡ መድበለ ፓርቲ ሰርዓት እና ሰብዓዊና ዲሞክራሲያዊ መብት- በእኔ ዕይታ - Zehabesha Amharic

የምርጫ ክርክር አንድ፡ መድበለ ፓርቲ ሰርዓት እና ሰብዓዊና ዲሞክራሲያዊ መብት- በእኔ ዕይታ - Zehabesha Amharic

ምን ታቅዶ ምን ተፈፀመ?፣ …የቀጣይ የትግል አቅጣጫ ምን ይሁን? (ኤርሚያስ ለገሰ) - See more at: http://www.zehabesha.com/amharic/archives/39782#sthash.rgXpPfTz.dpuf

ፍል አንድ) ምርጫ 2007 አስመልክቶ ገዥው መደብ “ምን አስቦ ምን ይፈጵማልdaniel ermias ” የሚ

አገር ወዳዱና አጥባቂ ኦርቶክሳዊ የነበረው አበበ ቢቂላ አስገራሚ የታሪክ ማስታወሻ ቪድዮ

አገር ወዳዱና አጥባቂ ኦርቶክሳዊ የነበረው አበበ ቢቂላ አስገራሚ የታሪክ ማስታወሻ ቪድዮ
++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++
የኃይሌ ገብረሥላሴና የአበበ ቢቂላ የደምጽ መመሳሰል በጣም ይገርማል:: አዳምጠው ይፍረዱ! 
. ኢትዮጵያ ውስጥ ሩጫና ኦሎምፒክ እንዲስፋፋ ንጉሰነገስት ኃይለሥላሴ ከባድ ማበረታቻ ያደርጉ ነበር:: በዘመናቸው ትልቅ ሽልማት ያገኙት አትሌቶች ነበሩ:: 
. ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ሻምበል አበበ ቢቂላ ሲያርፍ ሀገር አቀፍ የሀዘን አዋጅ አውጀው ነበር::ንጉሱ ጥብቅ ትዛዝ በማስተላለፋቸው የሻምበል አበበ ቢቂላን ቀብር ላይ 75,000 ሰው ተገኝቷል::
."አትሌት መሆን በቁምም ይሄን ያህል ካስሸለመ : በህልፈትም ይሄን ያህል ካስከበረ" በማለት በርካታ ኢትዮጵያውያን አትሌቲክስን እንዲቀላቀሉ ሆነ::

Monday, March 16, 2015

ኦህዴድ 25ኛ አመት በአሉን ለማክበር ለሚያደርገው ዝግጅት የመንግስት ሰራተኛውን ለቅስቀሳ አሰማራ

መጋቢት ፯(ሰባት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ኦህዴድ የ25ኛ አመት በአሉን በትግራይ ክልል ውስጥ ለማክበር የነበረው ፍላጎት ከተደናቀፈ በሁዋላ፣ በደራ ወረዳ ጉንዶመስቀል ከተማ ለማክበር ከፍተኛ ዝግጅት እያደረገ ሲሆን፣ የተለያዩ የመንግስት መስሪያ ቤቶች
ተዘግተው ሰራተኞች የገጠሩን ህዝብ እንዲቀሰቅሱ ተሰማርተዋል። መጋቢት 10 የመንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናት ጉንዶመስቀል ይገባሉ ተብሎ በመጠበቁ እጅግ በርካታ የፌደራል ፖሊስ አባላትና የደህንነት ሰራተኞች ወደ ከተማዋ ገብተዋል።
የመንግስት መስሪያ ቤቶች ተዘግተው ሰራተኞች ህዝቡን እንዲቀሰቅሱ ወደ ገጠር ተልከዋል።  የፊታችን ሀሙስ በሚከበረው ዝግጅት ላይ ከ10 ሺ በላይ ህዝብ ለመሰብሰብ ታስቧል።

Saturday, March 14, 2015

ትግሉን በየፈርጁ (የዋሺንግትንና አካባቢው የኢትዮጵያውያን የጋራ ግብረሃይል

March 13, 2015
የኢትዮጵያ የአንድነትና የዲሞክራሲ ሃይሎች በጠላት ጥቃት ደርሶባቸው ተጎድተው ተሸማቀው አንገታቸውን እንዲቀብሩ ሲገደዱ አድርባይ ሃይሎች በመድረኩ መቧረቃቸው የሚጠበቅ ነው፤ይህንን ጊዜያዊ ክስተት እንደዘላለማዊ ሃቅ የሚወስዱ ካሉ እጣ ክፍላቸው ተስፋ መቁረጥና ጨለምተኝነት ይሆናል። ከጨለማው ባሻገር የኮከቢቱን ብርሃን የሚያዩ ግን ለወያኔ ግፍ የማይበገሩ የሃቅን አቸናፊነት የኢትዮጵያን ትንሳኤ አይጠራጠሩም።

"ሕዝባዊ እምቢተኝነቱ ይቀጥል... ገንዘባችሁን ከሕወሓት ባንኮች ከወጋገንና አንበሳ ባንኮች አውጡ" - አርበኞች ግንቦት 7 - Zehabesha Amharic

"ሕዝባዊ እምቢተኝነቱ ይቀጥል... ገንዘባችሁን ከሕወሓት ባንኮች ከወጋገንና አንበሳ ባንኮች አውጡ" - አርበኞች ግንቦት 7 - Zehabesha Amharic

ጄኔራል ፃድቃንና ጤዛዋ ማሌሊት ...በ40ኛው - ከአረጋዊ በርሀ - Zehabesha Amharicበነገራችን ላይ ቺፍ ኦፍ ስታፉ ከጠላት የሚገኘው ስንቁም ትጥቁም 90% መሆኑ በኣሃዝ ከነገረን ዘንዳ በራሱ ድርጅት ለወገን ጦር የሚመደበው የስንቅና ትጥቅ መጠን ማወቅ እንዴት ይሳነዋል? “ቺፍ ኦፍ ስታፍ” ባጀቱ ካላወቀ ማን ሊያውቅለት ነው? - See more at: http://www.zehabesha.com/amharic/archives/39706…

ጄኔራል ፃድቃንና ጤዛዋ ማሌሊት ...በ40ኛው - ከአረጋዊ በርሀ - Zehabesha Amharic

Thursday, March 12, 2015

ESAT Eneweyay March 11, 2015 Ethiopia | ESATTUBE

ESAT Eneweyay March 11, 2015 Ethiopia | ESATTUBE

ESAT Managing Director a target of Cyber Spyware by the Ethiopian Regime

March 9, 2015
(The Washington Post) The Ethiopian government appears again to be using Internet spying tools to attempt to eavesdrop on journalists based in suburban Washington, said security researchers who call such high-tech intrusions a serious threat to human rights and press freedoms worldwide.
Neamin Zeleke, the managing director of Ethiopian Satellite Television
Neamin Zeleke, the managing director of Ethiopian Satellite Television
The journalists, who work for Ethiopian Satellite Television in Alexandria, Va., provide one of the few independent news sources to their homeland through regular television and radio feeds — to the irritation of the government there, which has accused journalists of “terrorism” and repeatedly jammed the signals of foreign broadcasters.

የጎሳ ፌዴራሊዝም መርዝ በኢትዮጵያ (ፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም)እራሱን ህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ (ህወሀት) እያለ የሚጠራው ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ የሀሰት እና የሸፍጥ የተውኔት መድረክ የተንጸባረቀበትን ህገመንግስት አርቅቆ እ.ኤ.አ ታህሳስ 8/1994 በማጽደቅ በኢትዮጵያ ህዝብ ጫንቃ ላይ ጫነ፡፡ በህገ መንግስቱ ሰነድ የመጀመሪያ መግቢያ መንደርደሪያ ላይ እንዲህ የሚል ጽሁፍ ሰፍሮ ይገኛል፣ ”እኛ የኢትዮጵያ ብሄሮች ብሄረሰቦች እና ህዝቦች…

March 11, 2015
ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም
ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ
እራሱን ህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ (ህወሀት) እያለ የሚጠራው ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ የሀሰት እና የሸፍጥ የተውኔት መድረክ የተንጸባረቀበትን ህገመንግስት አርቅቆ እ.ኤ.አ ታህሳስ 8/1994 በማጽደቅ በኢትዮጵያ ህዝብ ጫንቃ ላይ ጫነ፡፡ በህገ መንግስቱ ሰነድ የመጀመሪያ መግቢያ መንደርደሪያ ላይ እንዲህ የሚል ጽሁፍ ሰፍሮ ይገኛል፣ ”እኛ የኢትዮጵያ ብሄሮች ብሄረሰቦች እና ህዝቦች…
1ኛ) የብሄሮችን፣ ብሄረሰቦችን እና ህዝቦችን የእራስን ዕድል በእራስ ለመወሰን፣
2ኛ) ብሄሮች ብሄረሰቦች እና ህዝቦች የየእራሳቸውን አካባቢያዊ ግዛት እራሳቸው እንዲያስተዳድሩ እና የበለጸገውን እና የኩራታችን አሻራ የሆነውን የባህል ቅርሶቻቸውን በመያዝ በአንድነት እንዲኖሩ ለማስቻል፣
3ኛ) ለዘመናት ተንሰራፍተው የኖሩትን ፍትሀዊ ያልሆኑ ግንኙነቶችን ለማስተካከል፣ እና
4ኛ) አንድ የኢኮኖሚ ማህበረሰብ በመፍጠር ዕድገትን ለማፋጠን ይህ ህገመንግስት ተዘጋጅቷል” ይላል፡፡
አነጣጥሮ ለመመልከት ደግሞ የአሜሪካ ህገ መንግስት በመገቢያው አንቀጾች ላይ የሰፈረው መንደርደሪያ እንዲህ ይላል፣ “እኛ የዩናይትድ ስቴትስ አሜሪካ ህዝቦች እንከን የሌላት ሀገርን ለመፍጠር፣ ፍትህን ለማስፈን፣ የሀገር ውስጥ ሰላም እና ጸጥታን ለማስፈን፣ የጋራ መከላከያችንን ለማጠናከር፣ የህዝቡን የኑሮ ደህንነት ለማረጋገጥ እንዲሁም የእኛን እና የመጭውን ትውልድ ነጻነት ለመጠበቅ ሲባል ለዩናይትድ ስቴትስ አሜሪካ ይህንን ህገ መንግስት አዘጋጅተናል፡፡“The Poison of Ethnic Federalism in Ethiopia’s Body Politic
የህወሀት ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ህገ መንግስት የኢትዮጵያን ህዝቦች እንደ ከብት መንጋ በአካባቢ በመለያየት ወይም ደግሞ

ችሎቱን አሻንጉሊት ብለሃል የተባለው አብርሃ ደስታ ተጨማሪ 9 ወር ተፈረደበት * ፍርዱን ሲሰማ ለ3ኛ ጊዜ በማጨብጨብ አሻንጉሊቱን ችሎት "ደፈረ" - Zehabesha Amharic

ችሎቱን አሻንጉሊት ብለሃል የተባለው አብርሃ ደስታ ተጨማሪ 9 ወር ተፈረደበት * ፍርዱን ሲሰማ ለ3ኛ ጊዜ በማጨብጨብ አሻንጉሊቱን ችሎት "ደፈረ" - Zehabesha Amharic

“ችሎት ደፍራችኋል” ተደፋሪው “ፍርድ ቤት” * "እኛ የደፈርነው ችሎት አሻንጉሊት ችሎት ነው 'already' የተደፈረ ችሎት ነው" አብርሃ ደስታ * “ችሎቱ ላይ ያጨበጨብነው በማፌዝ ሳይሆን በምሬት ነው” የሺዋስ አሰፋ * “ችሎት ደፍራችኋል ካላችሁ ቅጣቱን ጨምሩብንና ሸኙን” ዳንኤል ሺበሽ * የተቃዋሚ ፓርቲዎች አመራሮች ቅጣት ተላለፈባቸው፣ ተጨማሪ ቅጣትም ይጠብቃቸዋል

“ችሎት ደፍራችኋል” ተደፋሪው “ፍርድ ቤት”
* "እኛ የደፈርነው ችሎት አሻንጉሊት ችሎት ነው 'already' የተደፈረ ችሎት ነው" አብርሃ ደስታ
* “ችሎቱ ላይ ያጨበጨብነው በማፌዝ ሳይሆን በምሬት ነው” የሺዋስ አሰፋ
* “ችሎት ደፍራችኋል ካላችሁ ቅጣቱን ጨምሩብንና ሸኙን” ዳንኤል ሺበሽ
* የተቃዋሚ ፓርቲዎች አመራሮች ቅጣት ተላለፈባቸው፣ ተጨማሪ ቅጣትም ይጠብቃቸዋል
http://www.goolgule.com/in-contempt-of-the-court/
በእነ ዘላለም ወርቃገኘሁ የክስ መዝገብ የሽብር ክስ ተመስርቶባቸው ከስምንት ወራት በላይ በእስር ላይ የሚገኙት የሰማያዊ፣ የአንድነት እንዲሁም የዓረና ትግራይ ፓርቲዎች አመራሮች “ችሎት በመድፈር ወንጀል” ጥፋተኛ በመባላቸው መጋቢት 1/2007 ዓ.ም በልደታ ከፍተኛው ፍርድ ቤት በዋለው ችሎት በሦስቱ አመራሮች ላይ እያንዳንዳቸው በሰባት ወራት እስራት እንዲቀጡ ተወስኖባቸዋል፡፡
የካቲት 26/2007 ዓ.ም ተከሳሾች በቂሊንጦ ማረሚያ ቤት የሰብዓዊ መብት ጥሰት እንደተፈጸመባቸውና ንብረትም እንደተወሰደባቸው በመግለጽ አቅርበውት ለነበረው አቤቱታ ፍርድ ቤቱ የማረሚያ ቤቱን ምላሽ ሙሉ ለሙሉ በመቀበል አቤቱታቸውን ውድቅ ማድረጉን ተከትሎ 5ኛ ተከሳሽ አቶ የሺዋስ አሰፋ በማጨብጨቡና 3ኛ ተከሳሽ አብርሃ ደስታና 4ኛ ተከሳሽ አቶ ዳንኤል ሺበሽ ሳይፈቀድላቸው “ጥሩ ፍርድ፣ ጥሩ ብይን” በማለት አቶ የሺዋስን በመደገፍ ችሎት ደፍረዋል ተብለው ጥፋተኛ መሰኘታቸው ይታወሳል፡፡
በዚህ መሰረት ፍርድ ቤቱ ለዛሬ የቅጣት ውሳኔ ለመስጠት ተሰይሞ በአብርሃ ደስታ፣ በየሺዋስ አሰፋ እና ዳንኤል ሺበሽ ላይ የሰባት ወራት እስራት በእያንዳንዳቸው ላይ ወስኗል፡፡ ሦስቱም ተከሳሾች ፍርድ ቤቱ የሰጠውን ውሳኔ በመቃወም ድጋሜ ችሎት ውስጥ አጨብጭበዋል፡፡ በዚህም ድጋሜ ጥፋተኛ ተብለዋል፤ ከሁለት ቀናት በኋላም የቅጣት ውሳኔ ይወሰንባቸዋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
ሦስቱ ተከሳሾች “እድል ስጡን እንናገር፣ አቤቱታም አለን ተቀበሉን” ቢሉም ፍርድ ቤቱ ሊሰማቸው አልፈለገም፡፡ በተለይ ዳንኤል ሺበሺ “ሌላ አቤቱታ አለኝ፣ ፍርድ ቤቱ ያዳምጠኝ” ብሏል፡፡ ፍርድ ቤቱ አሁንም ችሎቱ ላይ እያፌዛችሁ ነው በሚል ጥፋተኛ ሲላቸው ሦስቱም አመራሮች ፍርድ ቤቱን ማስፈቀድ ሳያስፈልጋቸው አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡
“እኛ የደፈርነው ችሎት አሻንጉሊት ችሎት ነው፡፡ ‘already’ የተደፈረ ችሎት ነው” ሲል አብርሃ ደስታ ተናግሯል፡፡ በዚህ ጊዜ ዳኞቹ ጣልቃ በመግባት፣ “የምትናገረው ነገር እንደገና ወደ ማዕከላዊ ወንጀል ምርመራ የሚወስድህ ጉዳይ ነው፤ ምርመራ ይደረግበታል” ሲሉ አብርሃ በበኩሉ “አሁንስ ቢሆን የምናገረውን ፖሊስ እየሰማ አይደለምን?” ሲል መልሷል፡፡
አቶ የሺዋስ አሰፋ በበኩሉ “ከስምንት ወር በላይ ታፍነናል፡፡ በህግ አይደለም የተያዝነው፡፡ ደግሞ ማጨብጨባችን በችሎቱ ከማፌዝ ሳይሆን ከምሬት በመነጨ ነው፡፡ ህገ-መንግስታዊ መብታችን ተጥሷል፡፡ እኔ ለምሳሌ የሰማያዊ ፓርቲ አባል በመሆኔ ነው የታሰርኩት” ብሏል፡፡
አቶ ዳንኤል ሺበሽ ደግሞ “አሁንም ችሎት ደፍራችኋል ካላችሁ ቅጣቱን ጨምሩብንና ሸኙን፡፡ በእርግጥ ዳኞች ላይ ያለውን ጫና እንረዳለን” ሲል ችሎት ውስጥ ተናግሯል፡፡
በዚህ ሁኔታ በተከሳሾችና በችሎቱ መካከል ያለው አለመግባባት ሲጨምር ዳኞቹ መጋቢት 3/2007 ዓ.ም ለሁለተኛ ጊዜ የቅጣት ውሳኔ እንደሚሰጥ በመጥቀስ ሦስቱ ተከሳሾች ከችሎት በፖሊስ እንዲወጡ ተደርገዋል፡፡ ከችሎት እየወጡ እያሉም አቶ ዳንኤል ሺበሽ “ፍትህ ተጠምተናል፤ ፍትህ ለኢትዮጵያ ህዝብ!” እያለ ችሎቱን ለቅቆ ወጥቷል፡፡
በሌላ በኩል ሦስቱ ተከሳሾች ከችሎት መውጣታቸውን ተከትሎ፣ ከዚህ ቀደም በማረሚያ ቤቱ ላይ በቀረበው አቤቱታ ዳኞች በሰጡት አስተያየት ላይ አቤቱታ አቅርቦ እንደነበር በማስታወስ አቤቱታው እንዲመዘገብለት የጠየቀው አቶ ሀብታሙ አያሌው፣ “በበኩሌ ያሉኝን መረጃዎች እያቀረብኩ ስነ-ስርዓቱን አክብሬ ክርክሩን አቀጥላለሁ” ሲል ተናግሯል፡፡ (ነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር የተዘገበውን ከነገረ ኢትዮጵያ ፌስቡክ ገጽ የተገኘ)

የዲሞክራሲዊለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት በኖርዌይ  ድጋፍ አሰባሳቢ ጊዜያዊ ግብረ ኃይል የተሰጠ የአቋም መግለጫ  !!       

የዲሞክራሲዊለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት በኖርዌይ  ድጋፍ አሰባሳቢ ጊዜያዊ ግብረ ኃይል የተሰጠ የአቋም መግለጫ  !!       

Wednesday, March 11, 2015

የISIS ቡድን ነፍሰ ገዳዩ ጆን፣ ትውልደ ኢትዮጵያዊ የቅርብ ጓደኛ አዲስ አበባ ውስጥ ታስሯል መባሉ እያነጋገረ ነው - Zehabesha Amharic

የISIS ቡድን ነፍሰ ገዳዩ ጆን፣ ትውልደ ኢትዮጵያዊ የቅርብ ጓደኛ አዲስ አበባ ውስጥ ታስሯል መባሉ እያነጋገረ ነው - Zehabesha Amharic

ማስተርስ/ዶክተሬት እንደ መለዋወጫ እቃ! (ታሪኩ አባዳማ) - Zehabesha Amharicማስተርስ/ዶክተሬት እንደ መለዋወጫ እቃ! (ታሪኩ አባዳማ) 413 EmailShare ታሪኩ አባዳማ | የካቲት 2007 ልጄ አስራ ሁለተኛ ክፍል ስለጨረሰ የደስታዬ ተካፋይ ትሆኑ ዘንድ… የሚል ግብዣ ደርሷችሁ አያውቅም? እናንተም ፋሽኮ ቪኖ ወይንም እናትና ልጅ አረቄ ይዛችሁ ድግሱን ለማድመቅ ሳትሄዱ አልቀራችሁም – የዚያን ዕለት ጎረምሶቹ የቀለጠ ፓርቲ ደግሰው እስኪነጋ ይጨፍራሉ አሉ… ይህስ ይሁን። - See more at: http://www.zehabesha.com/amharic/archives/39546#sthash.GPYsNQ27.dpuf

ማስተርስ/ዶክተሬት እንደ መለዋወጫ እቃ! (ታሪኩ አባዳማ) - Zehabesha Amharic

ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ሦስት የመንግሥት ተቋማትን አስጠነቀቁ‹የውኃ ሥራዎች በሞትና በሕይወት መካከል ያለ ዘርፍ ነው›› ‹‹ማኘክ ከሚችሉት በላይ የጎረሱ ስላሉ ጀርባቸውን በመምታት ማስወጣት ይገባል›› - See more at: http://satenaw.com/amharic/archives/5273#sthash.ck0Osz75.dpuf

ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ሦስት የመንግሥት ተቋማትን አስጠነቀቁ

ESAT DC Daily News 09 March 2015ed - Zehabesha - Latest Ethiopian News Provider

ESAT DC Daily News 09 March 2015ed - Zehabesha - Latest Ethiopian News Provider

Monday, March 9, 2015

The Washington Post, ESAT Managing Director a target of Cyber Spyware by the Ethiopian Regime - Zehabesha - Latest Ethiopian News Provider

The Washington Post, ESAT Managing Director a target of Cyber Spyware by the Ethiopian Regime - Zehabesha - Latest Ethiopian News Provider

የ300 ሚሊየን ብር እርዳታ ለጤና ጣቢያ ግንባታ…የተባለውን ቅርጥፍ…

የ300 ሚሊየን ብር እርዳታ ለጤና ጣቢያ ግንባታ…የተባለውን ቅርጥፍ…..
መርካቶ ሲኒማ ራስ የዛሬን አያርገውና ገናናው አሜሪካን ግቢ ድሀዎችን በልማት ስም በማስነሳት/ጤና ጣቢያ ልንገነባ ነው ብለው ያፈናቀሉትን ህብረተሰብ ወደ ጎን አድርገው ዛሬ ኡራጎ የንግድ ማዕከል የሚል ሰርተውበት በሙስና በልጽገው ጠፍተዋል፡፡ ይህ ህንጻ ለማሰራት ተነሺዎችን ጤና ጣቢያ ሊሰራ ነው ለልማት ነው ብለው ካስነሱ በኋላ በብዙ ሚሊየን በሚቆጠር ብር መሬቱን ሽጠው አሁን የንግድ ማዕከል ሆኗል፡፡ በወቅቱ ግሎባል ፈንድ የተባለው ዓለም አቀፍ ድርጅት 300 ሚሊየን ብር እርዳታ ሰጥቶ የነበረ ቢሆንም ገንዘቡ የት እንደገባ አይታወቅም፡፡ የአሜሪካን ግቢ የኢህአዴግ ኮካዎች ላደረሱኝ መረጃና ፎቶ ከልብ አመሰግናልሑ፡፡ የስርዓቱን የሙስና ደረጃና አድሎአዊነት በየጊዜው እያጋለጥን ትግሉን ማቀጣጠል

Sunday, March 8, 2015

(ዜና ፎቶ) መርካቶ አካባቢ ያሉ ወጣቶች አዛውንቶችን እና የአእምሮ ህመም ያለባቸው የጎዳና ተዳዳሪዎችን ገላቸውን ሲያጥቡና ጸጉራቸውን ሲላጩ ዋሉ - See more at: http://www.zehabesha.com/amharic/archives/39641#sthash.myhXBOpL.dpuf

merkato addis ababa copy

( ወያኔ የረጨው መርዝ ) አማረ ፣ ኦሮሞ የሚሉት በሽታ - ግርማ ካሳ

( ወያኔ የረጨው መርዝ )
አማረ ፣ ኦሮሞ የሚሉት በሽታ - ግርማ ካሳ
እስቲ እነዚህን ፎቶዎች ተመልከቱ። አንዱ የኦነግ ካርታ ነው። ሌላው ደግሞ የአማራ መንግስት ብለው ያወጡት ነው። የኦነግ ካርታ እንዳለ ቀድሞ የሸዋ ክፍለ ሃገር ተብሎ የሚጠራዉን እንዲሁም በርካታ መሬቶች ከወሎ ያጠቃልላል። የአማራ መንግስት ካርታ ደግሞ የቀድሞ የቤጌምድር፣ የጎጃም፣ የሸዋና የወሎ ክፍለ ሃገራትን፣ አሁን ወደ ትግራይ በሃይል የተጠቃለሉ ሁምራ፣ ወልቃት፣ ጠገዴን ፣ ጨለምታና አላማጣን ያጠቃልላል።
የኦነግ ካርታ ከሞላ ጎደር አሁን ኦሮሚያ ተብል የምትጠራዋን በኋይል በሕዝቡ ላይ የተጫነችዋን ክልል ትመስላለች። ለምን ቢባል. ኦሮሚያ የምትባል ክልል ስትፈጠር፣ ኦነግ የመንግስት አካል ስለነበረ።

Saturday, March 7, 2015

ዲ/ን ዳንኤል ክብረት፣ አቶ ኤርሚያስ ለገሰና ኢህአዴግ

  • 68
     
    Share
Ermias Legesseከጀማል ሙሳ
«አክራሪ እስልምና የኢትዮጵያ ክርስትና አስቸጋሪው ፈተና» ብለህ ያዘጋጀኸውን ጥናታዊ ጽሁፍ አዳመጥኩት። አቶ ኤርሚያስ ለገሰ የሰጠህን ምላሽም እንዲሁ አነበብኩት። አንተም «ኤርሚያስ ሆይ!» ብለህ የጻፍከውን ምላሽ አንብቤ እንደጨረስኩ «ለዲያቆን ዳንኤል ክብረት የመጨረሻ አስተያየት» የሚለውን የኤርሚያስን ጽሁፍም አነበብኩት። ሁሉንም ካነበብኩ በሗላ ግን ባንተ ብቻ ሳይሆን ባገሬ መንግስትም በጣም አዘንኩኝ።
በርግጥ ኤርሚያስ ለገሰ በሰጠህ መልሶች ብዙዎችን የማውቃቸውን እውነታዎች ባገኛቸውም ካንተን ጥናታዊ ፅሁፍና የመልስ ፅሁፎች ግን አንተና የኢህአዴግ ባለስልጣናት ለኢትዮጵያ ሙስሊም ያላችሁን ትልቅ ጥላቻ ለመገንዘብ ችያለሁ። ያነሳሃቸውን ነጥቦች ስመለከት ከመጀመሪያው ጀምሮ ያቀረብከው ታሪክ ስለቁራአን ፤ስለነጃሽ ፤ስለኢትዮጵያውስጥ እስልምና

በኢህአዴግ መከላከያ ሰራዊት …

meeting 31 regiment about administrationማእከላዊ እዝ ውስጥ የአስተዳደር ችግር እየከፋ በመሄዱ ምክንያት የእዙ ሰራዊት ሃይለኛ ጥያቄ በማቅረብ ላይ እንደሚገኝ ከሰራዊቱ ውስጥ አፈትልኮ የደረሰን መረጃ ገለፀ፣
በማእከላዊ እዝ ከየካቲት 11 እስከ 18 /2007 ዓ/ም ጀምሮ በውስጣዊ የአስተዳደር ጉዳይ ላይ የሚመለከት ስብሰባ እንደተካሄደ የገለፀው መረጃው በስብሰባው ላይ በሰፊው ከተነሱት የአስተዳደር ችግሮችም ደመወዛችንም እንኳን ኑሯችን ልንመራበት ይቅርና ለአንድ ቀንም ሊሸፍንልንም አልቻለም ሲሉ ችግራቸው እንደገለፁ ለማወቅ ተችሏል፣
ሰራዊቱ በየመድረኩና በየወቅቱ እያቀረብናቸው ካሉት ችግሮቻችን መፍትሄ ለምን አይደረግላቸውም?” ሲሉ መጠየቃቸውንና በሰራዊቱ ውስጥ ከ24 ሰአት ጀምሮ እስከ አመታዊ ፍቃድ እንደተከለከለ በመግለፅ ሰራዊቱም ለምን ተከለከልን ብሎ በጠየቀበት ጊዜ በስብሰባው መሪዎች አወንታዊ ምላሽ ማግኘት እንዳለተቻለ መረጃው ጨምሮ አስረድቷል፣

እጩ ተወዳዳሪዎቻችን እየታሰሩ ናቸው – አምዶም ገብረስላሴ,ኣቶ ብርሃን ንጉስ ተክለዝጊ የተባሉ የዓረና-መድረክ የክልል ምክር ቤት እጩ ተወዳዳሪ ከነ ሚስታቸውና ታላቅ ልጃቸው ታሰሩ። - See more at: http://www.zehabesha.com/amharic/archives/39606#sthash.oEw1MCut.dpuf

ኣቶ ብርሃን ንጉስ ተክለዝጊ የተባሉ የዓረና-መድረክ የክልል ምክር ቤት እጩ ተወዳዳሪ ከነ ሚስታቸውና ታላቅ ልጃቸው ታሰሩ።
ኣቶ ብርሃን ንጉስ ተክለዝጊ በቖላ ተምቤን ወረዳ የወርቃ ኣምባ ምርጫ ክልል ዓረና-መድረክ ወክለው ለክልል ምክር ቤት እጩ ተወዳዳሪ ሁነው ቀርበዋል።
ይህ እስር የተፈፀመው በወረዳው ኣስተዳዳሪዎች፣ የሃይማኖት ኣባቶች፣ የቅርብ ዘመዶች ከውድድሩ እንዲወጡ የተሞከረው ልመናና ማባበል ሊቀበሉ ባለመቻላቸው ነው።
1545648_786839981400938_395658053806875682_nኣቶ ብርሃን ንጉስ ተኽለዝጊ በቖላ ተምቤን ወረዳ ስምረት ቀበሌ ለበርካታ ዓመታት ዋና ኣስተዳዳሪና የምሊሻ ኮማንደር ሁኖው ኣገልግለዋል። ኣስተዳዳሪ በነበሩበት ወቅት ከፍተኛ የህዝብ ፍቅር ያሳደሩ ሲሆን ከስልጣናቸው ሲወርዱም ያለ ህንዝብ ፍቃድ ከወረዳ የመጣ ትእዛዝ የተደረገ ነበር።
የወረዳው ኣስተዳዳሪዎች “.. ይህ ህዝባዊ ቅቡልነቱ ተጠቅሞ ዓረና-መድረክ እንዲያሸንፍ ያስችለዋል..” የሚል ስጋት በመፍጠሩ በማሳደራቸው በራሳቸው ትእዛዝ ዛሬ ዓርብ 27 / 06 / 2007 ዓ/ምኣቶ ብርሃን ንጉስ ተኽለዝጊ፣ ባለቤቱና ታላቅ ልጁ በጉያ እስር ቤት እንዲታሰር ኣድርገዋል።
የህወሓት መንግስት የመድረክ በኣፅቢ ወንበርታ እጩ ተወዳዳሪ የሆነው ኣቶ ወልደገብርኤል ሃይሉም “..የኣስር ወር እስር ተፈረደብህ..” በማለት ውቕሮ ወህኒ ቤት ማስገባታቸው የሚታወስ ነው።
የመድረክ እጩ ተወዳዳሪዎች እጅግ የከፋ የእስር ዛቻና እንግልት እያደረሱ ያሉ ወረዳዎች ጣንቋ ኣበርገለ፣ እምባ ኣላጀ፣ ኣፅቢ ወንበርታ፣ ቖላ ተምቤን፣ ታሕታይ ማይጨው፣ ዓዲ ግራት ናቸው።
በነዚህ ወረዳ የሚገኙ እጩ ተወዳዳሪዎቻችን ድብደባ፣ እስር፣ ወከባና እንግልት እየደረሰባቸው ይገኛል። እነዚህ ወረዳዎች ግፉ ያበዙት ብለን የገለፅናቸው እንጂ እንደ ደጉዓ ተምቤን የመሰሉ ወረዳዎችም “..ያለ የወረዳ የድጋፍ ደብዳቤት ቅስቀሳ የሚያካሂድ፣ በራሪ ወረቀት የሚያድል ሰው ካገኛቹ እርምጃ ውሰዱበት..” የሚል ትእዛዝ ለሚልሻዎች ያስተላለፉም ኣሉ።
ያሁሉ የምሊሻ የተኩስ ልምምድ ሲያካሂ የከረመው ዓረና-መድረክ ኣባላት ቅስቀሳ ሲያካሂዱ ኣልሞ ለመምታት ታሳቢ ኣድርጎ ነበር ማለት ነው።
በኢትዮዽያ ያለው የይስሙላ ምርጫው በትግራይ ያለው ሁኔታ ግን ጭራሽ የምርጫ ጭላንጭል እንዳይታይ ከፍተኛ ጥረት እያደረጉ ይገኛሉ።
ነፃነታችን በእጃችን ነው..!
- See more at: http://www.zehabesha.com/amharic/archives/39606#sthash.oEw1MCut.dpuf

Ethiopian PM slams Kiir-Machar for war, says world will use “all influences” to bring peace - See more at: http://www.zehabesha.com/ethiopian-pm-slams-kiir-machar-for-war-says-world-will-use-all-influences-to-bring-peace/#sthash.h6vQWnEQ.dpuf

March 07, 2015
Mesfin and Desalegn_1_2Ethiopia’s Prime Minister Hailemariam Desalegn called for international action at the “highest level” to end South Sudan’s civil war after a deadline for a peace agreement passed yesterday in his capital Addis Ababa.
Desalegn’s Friday statment, addressed to the South Sudanese people, may signal a shift in approach by the Intergovernmental Authority on Development (IGAD), the regional bloc led by the prime minister which is mediating the peace talks.
The United Nations and the African Union look to IGAD for guidance on using sanctions or other targeted measures to end the war.
But Desalegn said IGAD has not produced results of peace so will refer to the wider international community to take stronger action.
“Our efforts cannot continue unaltered and expect a different outcome.” he said. “The peace process must be reinvigorated and reformed. In the coming days, I will consult with my colleagues, the IGAD leaders, partners and friends in the region, on the continent, and beyond to agree a common plan of action.”
“At the the highest level, the world must speak with one voice on South Sudan…We will use all influence at our disposal to convince those that remain intransigent,” he said, without specifically mentioning sanctions or other targeted measures against war leaders.
War leaders abdicated “sacred duty”
Desalegn further said that Kiir and Machar have abdicated their responsibilities as leaders by continuing the war.
“Leadership is never easy, but continuing a war flagrantly disregards the interests of you, the people. It is an abdication of the most sacred duty leaders have to you, their people: to deliver peace, prosperity and stability,” he said.
“Both President Kiir and Dr. Riek Machar have assured the Leaders of the IGAD Member States that they are committed to peace. At the same time, there are individuals on both sides who continue to beat the drums of war,” he said.
Source- https://radiotamazuj.org/en/article/ethiopian-pm-slams-kiir-machar-war-says-world-will-use-all-influences-bring-peace
- See more at: http://www.zehabesha.com/ethiopian-pm-slams-kiir-machar-for-war-says-world-will-use-all-influences-to-bring-peace/#sthash.h6vQWnEQ.dpuf