Friday, March 13, 2015

ፓርቲዉ በምርጫዉ ለመሳተፍ አጩዎቹን ሰይሞ፤የመወዳደሪያ አላማዎቹን ለይቶ ዝግጅቱን አጠናቅቆ ነበር።በዚሕ መሐል ነዉ ፓርቲዉ በአቶ ግርማ ቋንቋ «ለመወዳደር አይደለም ዉድድር ለመመልከት እንኳን ያልተዘጋጁ» ላሏቸዉ ሰዎች የተሰጠዉ። - See more at: http://satenaw.com/amharic/archives/5296#sthash.x4BvuVWW.dpuf

Girma Seifuበኢትዮጵያ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ብቸኛ
 የተቃዋሚ ፓርቲ እንደራሴ የሆኑት አቶ ግርማ ሠይፉ በመጪዉግንቦት ሊደረግ በታቀደዉ ምርጫ እንደማይሳተፉ አስታወቁ።እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ ተቃዋሚዉን የኢትዮጵያ አንድነትለዲሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) በምክትል ፕሬዝዳንትነት ይመሩ የነበሩት አቶ ግርማ እንደሚሉት በምርጫዉየማይወዳደሩት የኢትዮጵያ መንግሥትና ገዢዉ ፓርቲ ኢሕአዴግ በፓርቲያቸዉ ላይ ባደረሱባቸዉ ተፅዕኖነዉ።በኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ ዉሳኔ የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትሕንየፓርቲነት ፍቃድና ዕዉቅና ያገኙት ወገኞችበአቶ ግርማ እምነት አንድነትን የሚወክሉ አይደሉም።

መስከረም፤ 2003 ጀምሮ-ብቸኛ ከሚል ቅፅል ጋር የምክር ቤት እንደራሴነቸዉ ሲጠቀስ-ሲዘገብ እዚሕ ደረሱ።በሕጉ-መሠረት ያሉበት ምክር ቤት-በመጪዉ መስከረም በሌላ እስከሚተካም የምክር ቤት እንደራሴነታቸዉ ከነቅፅላቸዉመቀጠሉ አይቀርም።አቶ ግርማ ሰይፉ።ከዚያ በሕዋላ ግንብቸኛ» የሚለዉን ቅፅል «የቀድሞዉ» በሚለዉ ለማስተካትእንደ ፖለቲካዉ ወግ በምርጫ ተወዳድረዉ እስኪሸነፉ ወይም ከፖለቲካዉ «ጡረታ» እሲከዉጡ አልጠበቁም።የ48 ዓመቱ ጎልማሳ በግንቦቱ ምርጫ-መወዳደሩን ይፈልጉታል ግንአይወዳደሩም።
«እኛ» የሚሉት የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነትን።ፓርቲዉ በምርጫዉ ለመሳተፍ አጩዎቹንሰይሞ፤የመወዳደሪያ አላማዎቹን ለይቶ ዝግጅቱን አጠናቅቆ ነበር።በዚሕ መሐል ነዉ ፓርቲዉ በአቶ ግርማ ቋንቋ«ለመወዳደር አይደለም ዉድድር ለመመልከት እንኳን ያልተዘጋጁ» ላሏቸዉ ሰዎች የተሰጠዉ።
1997 ምርጫ ዉጤት የቀሰቀሰዉ ደም አፋሳሽ ዉዝግብ የኢትዮጵያ ተቃዋሚ ፓርቲዎችን ሕብረት፤ ጉልበትናእዉቅና አሳጥቶ በጣለ ማግሥት እንዳዲስ ከተደራጁት ፓርቲዎች ሰፊ ተቀባይነት፤ ብዙ አባላት ጠንካራ ፖለቲከኞችንካሰባሰቡ ጥቂት የፖለቲካ ማሕበራት አንዱ-አንድነት ነበር።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በአንድነትፖለቲከኞች መካካል የተነሳዉን ክፍፍል አስታኮባሳለፈዉ ዉሳኔ ከተወዛጋቢዎቹ ለአንዱ አዉቅናሰጥቷል።አቶ ግርማ «ክፍፍል» የሚለዉንአይቀበሉትም።ዉሳኔዉንም «ሕገ-ወጥ» ይሉታል።
547 በመቀመጫዎች ባሉት ምክር ቤት የተቃዋሚፓርቲ ብቸኛዉ ተወካይ በመሆን እስካሁን ያከናወኑትንተግባር ጥሩ መጥፎነት አቶ ግርማ «ተመልካች ነዉፈራጁ ይላሉ።«ያቅሜን አድርጌያለሁ» አከሉ እንደራሴዉ።
ነጋሽ መሐመድ
አርያም ተክሌ

No comments:

Post a Comment