Saturday, March 7, 2015

አርቲስት ብርሃኑ ተዘራ ሰማያዊ ፓርቲ ‹‹ወገኔ›› የተሰኘውን ሙዚቃ እንዲቀሰቅስበት ፈቀደ

አርቲስት ብርሃኑ ተዘራ ሰማያዊ ፓርቲ ‹‹ወገኔ›› የተሰኘውን ሙዚቃ እንዲቀሰቅስበት ፈቀደ
አርቲስት ብርሃኑ ተዘራ በቅርቡ ‹‹ወገኔ›› በሚል ያወጣውን ዜማ ሰማያዊ ፓርቲ ለቅስቀሳ እንዲጠቀምበት መፍቀዱን ለፓርቲው በላከው ደብዳቤ ገልጾአል፡፡ ኤፍ ኤም 96.3 ሰማያዊ ፓርቲ ለቅስቀሳ በላከው መልዕክት ላይ በማጀቢያነት የተጠቀመበት ሙዚቃ የባለ መብቱን ፈቃድ አላገኘም በሚል የቅስቀሳ መልዕክቱን መመለሱ ይታወሳል፡፡ በተመሳሳይ የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢብኮ) የሰማያዊ ፓርቲን የምርጫ ቅስቀሳ መልዕክት ‹‹እንደገና አስተካክሎ ካልላከ ለማስተላለፍ እቸገራለሁ›› በሚል መመለሱን ለፓርቲው በፃፈው ደብዳቤ አስታወቀ፡፡
ሰማያዊ ፓርቲ ‹‹በ2007 ዓ.ም አዲስ ላወጡት ‹‹ወገኔ›› የተሰኘው ነጠላ ዜማ ያለውን አክብሮት እየገለፀ፣ እርስዎ በስራዎ የገለጹትና ፓርቲውም የሚታገልላት አንድነቷ የተጠበቀላት ኢትዮጵያ እንድትኖር ለሚሰራው ስራ ይጠቀምበት ዘንድ ሙዚቃውን እንዲፈቅዱልን በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡›› ብሎ በደብዳቤ በጠየቀው መሰረት አርቲስቱ ፓርቲው ‹‹ወገኔ›› የተሰኘውን ዜማ ለቅስቀሳ እንዲጠቀምበት መፍቀዱን ገልጾአል፡፡
አርቲስ ብርሃኑ ተዘራ ለሰማያዊ በፃፈው ደብዳቤ ‹‹ሰማያዊ ፓርቲ ‹ወገኔ› የተሰኘውን ሙዚቃዬን ለመጠቀም የጠየቀኝን ፈቃድ በሙሉ ፍላጎቴ መፍቀዴን በፊርማዬ አረጋግጫለሁ፡፡›› ሲል ገልጾአል፡፡

No comments:

Post a Comment