Monday, May 9, 2016

የሺዋስ አሰፋና ዳንኤል ሺበሺ ከትንሿ እስር ቤት ወደ ትልቁ እስር ቤት ተቀላቅለዋል።

አብርሃም ደሰታ ከሁለት እንደሚቀረው ሰምተናል። መቼም ተፈተዋል ሲባል ደስ ይላል፤ ምክንያቱ በህወሓት እጅ ውስጥ ታስሮ መታረም ሳይሆን መሰቃየት ብለው ይቀለኛል። ያለጥፋታቸው ጥፋተኛ ናቹ በማለት ለእስርና ለእንግልት እየዳረጋቸው ይህን ፋሺስት ስርዓት እኔ በግል በጣም አጥብቄ እቃወመዋለሁ።
ዜጎች የመናገርና የመፃፍ እንዲሁም የመደራጀት መብት በሌላቸው ሁኔታ ላይ እስርና እንግልቱ እጅግ በጣም በዝቶል። አሁን ላይ ብዙ ወጣቶች በተለይ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በፖለቲካው ዘርፍ የሚንቀሳቀሱ ልጆች እየታደኑ ለእስር እየተዳረጉ ነው። ታስረው ከተፈቱም በኋላ ለመስራትም ሆን ከሀገር እንዳይወጡ እየተደረገ ያለበት ሁኔታ ነው። እነዚህ ልጆች በሀገራቸው ላይ ተቀጥረው ካልሰሩ እንዴትስ ነው ቤተሰቦቻቸውን ሊያስተዳድሩ የሚችሉት? እንዴትስ ነው እንደ አንድ ዜጋ መብታቸው ተከብሮ የሚኖሩት? አሁንም ቢሆን ይህን የከረፋ ስርዓት ከህዝባችን ላይ እስካልተወገደ ድረሰ የዜጎች በሰላም ወቶ መግባቱ እጅግ አሳሳቢ ነው።

No comments:

Post a Comment