Tuesday, November 11, 2014

የታፈኑት የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች ወደ ማዕከላዊ መዛወራቸው ተሰማ


Tensaye ከአንድ ሳምንት በፊት በየ ክፍለ ሀገሩ በገዥው ፓርቲ የደህንነት ኃይሎች የታፈኑት የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች ወደ ማዕከላዊ መዛወራቸውን የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች ገለጹ፡፡ በሰሜን ጎንደር ዞን የሰማያዊ ፓርቲ ሰብሳቢ የሆነው አቶ አግባው ሰጠኝ እንዲሁም፤ በዚሁ በሰሜን ጎንደር ዞን የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ አመራር አቶ አንጋው ተገኝ በትናንትናው ዕለት ወደ ማዕከላዊ መዛወራቸውን የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች ጠቅሰዋል፡፡

ሰሞኑን በየ ክፍለ ሀገሩ በገዥው ፓርቲ የደህንነት ኃይሎች የታፈኑት የሰማያዊ፣ የአንድነት፣ የመኢአድና የአረና አመራሮችና አባላት የደረሱበት ሳይታወቅ የቆየ ሲሆን ከትናንትና ጀምሮ ወደ ማዕከላዊ እየተዛወሩ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡

No comments:

Post a Comment