Monday, March 21, 2016

Ethiopia: “Double Digit” Economic Growth – Reality Check

Ethiopia’s annual harvest of shame. How the current starvation of 15 million Ethiopians unravel the deception of Ethiopia’s “double digit” economic miracle. Famine doesn’t give a hoot to the regime’s cooked rosy statistics nor does to its western media propagandistsEthiopia’s annual harvest of shame. How the current starvation of 15 million Ethiopians unravel the deception of Ethiopia’s “double digit” economic miracle. Famine doesn’t give a hoot to the regime’s cooked rosy statistics nor does to its western media propagandists
The statements presented a very rosy picture of Ethiopia and hid the income inequalities, adjunct poverty and dismal standard of living that persist. Today, the regime and its partners are forced to admit and present the true state of the Ethiopian economy and its effects on the majority of the population, of which 15 million are now in need of food aid.
Ethiopia touted as the “powerhouse in the Horn” is once again begging the international community to feed its people.
To prove that things had changed in Ethiopia, even Bob Geldof,

በኤርትራ እና በዙሪያዋ ለስለላ ስራ እንዲሁም ለቅኝት የዉጊያ ስምሪት እንዲጠቅሙ ተብለዉ የተሰማሩ የህወሃት ወታደራዊ መረጃ አባላቶች እየታደኑ መታፈናቸዉን የሚያረጋግጡ መረጃዎች አፈትልከዉ ወጥተዋል።


በተልይም ሞላ አስገዶም ከኤርትራ ወደ ህዉሃት ከፈረጠጠ ወዲህ በኤርትራ እና በኢትዮጵያ ነጻነት ሐይሎች የደህንነት ክትትል ምክንያት በህወሃት መረጃ ሰንሰለት ስር የነበሩ ሰላዮች በሙሉ መረሸናቸዉን የወያኔ ወታደራዊ ደህንነት በማረጋገጥ ለመከላከያ ሚኒስቴሩ እና ለሚመለከታቸዉ የደህንነት ክንፎች አሳዉቋል።
ወታደራዊ ደህንነቱ ሌሎች በተለያየ ምክንያት ወደ ኤርትራ ሰርገዉ እንዲገቡ የተደረጉ የስለላ ሰዎች በተለይም የአርበኞች ግንቦት ሰባትን አጠቃላይ ፖለቲካዊና መሰረታዊ የአደረጃጀት እርከን፣ እንዲሁም ወታደራዊ ኮርሶችና ዲስፕሊኖችን፣ ስልታዊ መዋቅርንና አቀማመጥን ለመሰለል እንዲረዱ ከተሰማሩ ግለሰቦች ዉስጥ አንዳቸዉም የት እንደገቡ ለማወቅ ያለመቻሉን ምንጮቻችን ጠቅስዋል።
ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ወደ ዉጊያዉ አምድ ከተቀላቀሉ ወዲህ ከኤርትራ ወደ ኢትዮጵያ በፍጥነት እየአሰገሰ በመምጣት ላይ የሚገኘዉን የለወጥ ነዉጥ መቛቋም የተሳነዉ የትግራይ ነጻ አዉጭ ቡድን ወታደራዊ ደህንነት የአርበኞች ግንቦት7ን እና የጥምር ሐይሎችን እንቅስቃሴ ማወቅ እንኳ እንደተሳነዉ በወታደራዊ የደህንነት ስልትም መበለጡን በተለይም የተሳሳቱ መረጃዎች እየደረሱት ላም ባልዋለበት... ሲቅበዘበዝ የነጻነት ሐይሎቹ ሽምቅ ዉጊያ ሰለባ እየሆነ መምጣቱን ለተደራቢ አዛዡ ሌተናንት ጄኔራል ዮሃንስ ገብረመስቀል ውይይት እንዲደረግበት ከቀረበው አጀንዳ ለመረዳት ተችሏል።
ስርአቱ አሁን ባጋጠመዉ የመረጃ መዳፈን ምክንያት ስጋት ላይ ስለወደቀ ድንገተኛና የተጠናከረ ተመላላሽ ጥቃት እንዲሰነዘር እንዲሁም በጎንደር ዙሪያ የሚገኘዉ የመከላከያ ሰራዊት በእጅጉ እንዲጠናከር ለማድረግ ከሸዋሮቢት የመጡ አዲስ ወታደሮች ወደ ክፍለ ጦሮቹ እንዲካተቱ እና አጥቂዉ የግንባር ሐይል ለመመሪያ ዝግጁ እንዲሆን በአመራሮች ቢወሰንም ከተራ ወታደር አንስቶ እስከ ከፍተኛ አመራሮች መመሪያ ለመቀበል ስጋት ላይ ናቸዉ።
ይህን መረጃ አያይዘዉ የላኩልን ምንጮች በኤርትራ የሚገኙ የነጻነት ሐይሎች ከምንዜዉም በበለጠ በንቃትና በመጠናከር እየወደቀ የሚገኘዉን ባለ ሁለት እግር ዝሆን ለመጣል እንዲዘጋጁ መዘናጋትን ፈጽመዉ እንዳያስቡት አስጠንቅቀዋል።
ከአራት እግሮቹ ሁለት የፊት እግሮቹን የቆሰለ ዝሆን ለመጣል ዝሆን መሆን አያስፈልግም።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ ! !
በኤርትራ እና በዙሪያዋ ለስለላ ስራ እንዲሁም ለቅኝት የዉጊያ ስምሪት እንዲጠቅሙ ተብለዉ የተሰማሩ የህወሃት ወታደራዊ መረጃ አባላቶች እየታደኑ መታፈናቸዉን የሚያረጋግጡ መረጃዎች አፈትልከዉ ወጥተዋል።
በተልይም ሞላ አስገዶም ከኤርትራ ወደ ህዉሃት ከፈረጠጠ ወዲህ በኤርትራ እና በኢትዮጵያ ነጻነት ሐይሎች የደህንነት ክትትል ምክንያት በህወሃት መረጃ ሰንሰለት ስር የነበሩ ሰላዮች በሙሉ መረሸናቸዉን የወያኔ ወታደራዊ ደህንነት በማረጋገጥ ለመከላከያ ሚኒስቴሩ እና ለሚመለከታቸዉ የደህንነት ክንፎች አሳዉቋል።
ወታደራዊ ደህንነቱ ሌሎች በተለያየ ምክንያት ወደ ኤርትራ ሰርገዉ እንዲገቡ የተደረጉ የስለላ ሰዎች በተለይም የአርበኞች ግንቦት ሰባትን አጠቃላይ ፖለቲካዊና መሰረታዊ የአደረጃጀት እርከን፣ እንዲሁም ወታደራዊ ኮርሶችና ዲስፕሊኖችን፣ ስልታዊ መዋቅርንና አቀማመጥን ለመሰለል እንዲረዱ ከተሰማሩ ግለሰቦች ዉስጥ አንዳቸዉም የት እንደገቡ ለማወቅ ያለመቻሉን ምንጮቻችን ጠቅስዋል።
ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ወደ ዉጊያዉ አምድ ከተቀላቀሉ ወዲህ ከኤርትራ ወደ ኢትዮጵያ በፍጥነት እየአሰገሰ በመምጣት ላይ የሚገኘዉን የለወጥ ነዉጥ መቛቋም የተሳነዉ የትግራይ ነጻ አዉጭ ቡድን ወታደራዊ ደህንነት የአርበኞች ግንቦት7ን እና የጥምር ሐይሎችን እንቅስቃሴ ማወቅ እንኳ እንደተሳነዉ በወታደራዊ የደህንነት ስልትም መበለጡን በተለይም የተሳሳቱ መረጃዎች እየደረሱት ላም ባልዋለበት... ሲቅበዘበዝ የነጻነት ሐይሎቹ ሽምቅ ዉጊያ ሰለባ እየሆነ መምጣቱን ለተደራቢ አዛዡ ሌተናንት ጄኔራል ዮሃንስ ገብረመስቀል ውይይት እንዲደረግበት ከቀረበው አጀንዳ ለመረዳት ተችሏል።
ስርአቱ አሁን ባጋጠመዉ የመረጃ መዳፈን ምክንያት ስጋት ላይ ስለወደቀ ድንገተኛና የተጠናከረ ተመላላሽ ጥቃት እንዲሰነዘር እንዲሁም በጎንደር ዙሪያ የሚገኘዉ የመከላከያ ሰራዊት በእጅጉ እንዲጠናከር ለማድረግ ከሸዋሮቢት የመጡ አዲስ ወታደሮች ወደ ክፍለ ጦሮቹ እንዲካተቱ እና አጥቂዉ የግንባር ሐይል ለመመሪያ ዝግጁ እንዲሆን በአመራሮች ቢወሰንም ከተራ ወታደር አንስቶ እስከ ከፍተኛ አመራሮች መመሪያ ለመቀበል ስጋት ላይ ናቸዉ።
ይህን መረጃ አያይዘዉ የላኩልን ምንጮች በኤርትራ የሚገኙ የነጻነት ሐይሎች ከምንዜዉም በበለጠ በንቃትና በመጠናከር እየወደቀ የሚገኘዉን ባለ ሁለት እግር ዝሆን ለመጣል እንዲዘጋጁ መዘናጋትን ፈጽመዉ እንዳያስቡት አስጠንቅቀዋል።
ከአራት እግሮቹ ሁለት የፊት እግሮቹን የቆሰለ ዝሆን ለመጣል ዝሆን መሆን አያስፈልግም።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ ! !

Documentary about Andargachew

ሰበር ዜና – በዳንሻ ግጭት ተፈጥሯል። በትግራይ ልዩ ፖሊስና በወልቃይቶች መሀል የተኩስ ልውውጥ ተደርጓል በትግራይ ልዩ ፖሊስና በወልቃይቶች መሀል የተኩስ ልውውጥ ተደርጓል መንገዶች ተዘግተዋል። በአቅራቢያ ባሉ መንደሮች የሚገኙ የወልቃይት ነዋሪዎች ተቃውሞ እያሰሙ ነው።


አቶ ሲሳይ ብርሃኔ የተባለ ወጣት ከሁለት ቀናቶች በፊት ከሚኖርበት ዳንሻ ከተማ በታጣቂዎች ታፍኖ መወሰዱን የሰሙት የወልቃይት ጠገዴና የአካባቢው ህዝብ ሲሳይ የተወሰደበትንና የሚገኝበትን ሁኔታ የዳንሻ ከተማ አስተዳደርን ሲጠይቁ ቆይተዋል፡፡ባለትዳርና የሁለት ልጆች አባት መሆኑ የተነገረለት ሲሳይ የወልቃይትን አማራነት በይፋ በመናገር ለወቅታዊው እንቅስቃሴም ድጋፉን እንደሚሰጥ መታወቁ ለአፈናው ምክንያት ሳይሆነው እንዳልቀረ ተገምቷል፡፡
ከዛሬ ረፋድ ጀምሮም በሲሳይ ጉዳይ ምላሽ ከአስተዳደሩ ያጡ የወልቃይትና የአካባቢው ነዋሪዎች ወደ ዳንሻ በማምራት የከተማይቱን አስተዳደርና የፖሊስ ጣብያዎችን መውረራቸውን መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ወደከተማይቱ የሚያስገቡ መንገዶች በተቃውሞ ምክንያት የተዘጉ ሲሆን ተቃውሞውን ለመቀላቀል ከአርማጭሆ ጭምር በዛ ያሉ ሰዎች ወደዳንሻ ለመምጣት እንቅስቃሴ መጀመራቸው ይነገራል፡፡
sisay
አቶ ሲሳይ ብርሃኔ
በዳንሻና ሶሮቃ ማምሻውን የታጠቁ የትግራይ ክልል ፖሊሶችና ሚሊሻዎች በብዛት በመግባታቸውም ከፍተኛ የተኩስ ልውውጥ እየተደረገ መሆኑን ከአካባቢው የተገኙ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ዳንሻዎች በስርዓቱ ያልታጠቁ ከዚህ ቀደም ነበራቸውንም ትጥቅ በመፍታት ሰላማዊ ኑሮ የጀመሩ በመሆናቸው ምሽቱን የገባውን ታጣቂ ኃይል መከላከል አለመቻላቸውም ተነግሯል፡፡

አካባቢው ከወልቃይት የማንነት ጥያቄ ጋር ተያይዞ ከፍተኛ ውጥረት የነገሰበት በመሆኑም የዛሬው የዳንሻና ሶሮቃ የተኩስ ልውውጥና የወጣቱ ታፍኖ መወሰድ ውጥረቱን ሊያፈነዳው እንደሚችል ይገመታል፡፡

Sunday, March 20, 2016

የህወአትን አላማ አላስፈጽምም Fredom Ethiopia



ጊዜው በኢትዮ ኤርትራ ጦርነት ወቅት ነበር።ወያኔ የሚይዘው የሚጨብጠው በጠፋበት በዚያ የጭንቅ ቀን ራቁታቸውን ያሰናብውታቸውን የቀድሞወ የሀገር መከላከያ ሰራዊት ከየቦታው ሲሰበስብ ጨርቅ ብሎ ያዋረደውን ባንዲራ ከተጣለበት ትቢያ አንስቶ በማራገፍ የሀገር ፍቅር ያለው ለመምሰል ሞከረ።የክሱም ሀውልት ለውላይታው ምኑ ነው የተባለው ህዝብም ዛሬ ሀገርህ ተወረረች ደርሰህ ታደራት የሚል ነገሪት ተጎሰመ።ሁሌም ለእስራት እና ለገደያ ለሰደት የሚታጩት የኦሮሞ እና የአማራ ተወላጆችም ሀገራቸውን ይከላከሉ ዘንድ በወጉ ጥሪው ቀረበላቸው።አርቲስቶች እና ታዋቂ ሰዎችም እንዲሁ።እኔም ከመሰራበት መስሪያ ቤት በግዴታ እንደዘምት ትእዛዝ ተላለፈልኝ።ይህን ያስተላለፈው የወረዳው አደረጃጀት ሀላፊ ግን የእርሱ ሀገር እንዳልሆነች ሁሉ እኔ ሂጀ በምሰዋው ህይወት እሱና ህወአት ስልጣን ላይ ለመቆየር ሲመኝ ለመዝመት ግን ፍላጎት የለውም ነበር።በዚህም የተነሳ ግማሽ ቀን የፈጀ ክርክር አድርጌ የማልሄድ ከሆነ ከስራ እንድሰናበት ወሰኑብኝ።እኔ ግን ለጊዜው በእነሱ ውሳኔ ስራየን ከምለቅ እስከመጨረሻው ያለውን ሁኔታ ባሉት መንገድ ተጉዠ መከታተሉን መረጥኩ።ወደ ሁርሶ ማሰልጠኛም ገባሁ።እዚህ ማሰልጠኛ ምንም አይነት አካዳሚያዊ ብቃት የሌላቸው የአንድ ብሄር ሰዎች የተሰበሰቡበት የአሰልጣኝነት ስነምግባር የጎደላቸው ሰዎች መሆናቸውን በነበረኝ ቆይታ ለማረጋገጥ ችያለሁ።
ወደ ማሰልጠኛው ለመሄድ ዋንኛው ምክንያቴ በኔ የህይወት መስዋእትነት መለስ እና ጀሌዎቹን ስልጣን ላይ ለማቆየት አልነበረም።ስራየን ሳላጣ እንዴት መቆየት እችላለሁ የሚለው እንጂ።በዚህ መሰረት ሶስት አመራጭ መንገዶች ተለምኩ።የመጀመሪያው ከስልጠናው ቦታ ለመዝመት ፈቃደኝነት እንደሌለኝ የመጣሁት ተገድጄ መሆኑን በማስረዳት እንዲመልሱኝ እና ወደ ሰራየ እንድመለስ እድል ይኖረኛል ከሚል ነበር።ይህ ሙከራ ሳይሳካ ቀረ።ስልጠናውንም ተከታትየ ጨረስኩ።ቀሪው ምደባ ነው።በምደባም የተሻለ ቦታ ካለ እዚያው እየሰራሁ ወላጆቼን አግዛለሁ የሚል እሳቤ ነበረኝ።ይህ እቅደም አልተሳካም።ቀሪ ሁለት እቅዶች አሉ።በምንም መልኩ ለማላምንበት ጦርነት የህይወት መስዋእትነት መክፈል እንደሌለብኝ ወስኛልሁ።በዚህም መሰረት ከተሳካ ለመንገድ ላይ ለመጥፋት ካልተቻለ ለመማረክ ካልሆነ ደግሞ በሚሰጠኝ መሳሪያ የስርአቱ ታማኝ ወታደራዊ ባለስልጣኖችን አጥፍቼ ለመጥፋት ውጥን ሀሳቤን ይዠ ከአዲስ አበባ ተነስተን ወደ ትግራይ ጉዞ ተጀመረ።እኔም የተሰጠኝን ወታደራዊ ልብስ ቀደም ብየ ውሃ ነከርኩት።በጠዋት ሁሉም ወታደራዊ ልብሱን ለብሶ ወደተመደበበት አውቶቡስ ሲገባ እኔ በውሃ የራሴ ፋቲኬን በኩርቱ ፔስታል ግጥም አደርጌ አስሬ በሲቭል ልብስ ወደአውቶቡሱ ሳመራ በጥያቄ አዋከቡኝ።እኔም አጥቤው ስለነበር እንዳለደረቀልኝ ነገርኳቸው።እነሱ ግን ጥያቄያቸው ሲደጋገም ልብሳችን ሳይሆን ልባችን ነው መመሳሰል ያለበት አልኳቸው።የልብስ መመሳሰል ምንም ጥቅም እንደሌለው ስነግራቸው ተቀበሉት።ጉዞውም ተጀመረ።እኔም በእቅዴ መሰረት ከሚሴ ላይ ለአዳር ከመኪናችን ስንወርድ ጉዞየን ወደ ኮንቦልቻ በሌሊት ብቻየኝ ጀመርኩ።ብዙ ከተጓዝኩ በኋላ አንድ ከአዲስ አበባ የሚመጣ መኪና አስቁሜ ትብብር ጥይቄው ውቧ ኮንቦልቻ አደረሰኝ።ይህ ሰው ምግብ እና ቢራም ግብዞኛል።እድሜህን ያርዝመው።በበነጋታውም በታክሲ ተሳፍሬ ደሴ ገባሁ።ከደሴ ባህርዳር።ደህና ሁኝ ወያኔ ብየ ተለያየን።ይኸው ያኔ የተቀደደው የኔና የወያኔ የጋብቻ ወረቀት እስካሁን ቀጥሏል።ዛሬ በዚያ ሰራዊት ውስጥ ስንት ልብሱ ብቻ የሚመሳሰል ሀሳቡ የተለያየ የሰራዊት አባል ይኖር ይሆን?እስከ መቼ ነው በይሉኝታ ተሸብበን ወገናችንን እየገደልን በኛ ህይወት እነሱ የተንደላቀቁ ህይወት እንዲኖሩ የምንፈቅደላቸው?
Fredom Ethiopia

የወቅታዊ ተግባራዊ ትግል (ወተት) መልዕክት: በግልጽ ጦርነት ውስጥ ካልሆን በህቡዕ ጦርነት እንሳተፍ ! (ክፍል 4: የመጨረሻ) ዶ/ር ታደሰ ብሩ


እያንዳንዱ ነፃነት ናፋቂ ኢትዮጵያዊ ሊሳተፍባቸው ከሚችሉ የህቡዕ ጦርነት ስልቶች ውስጥ አሻጥር፣ የስነ-ልቦና ጦርነት፣ የኢኮኖሚ ጦርነት፣ እና ኢህአዴግን እርስበርሱ ማናከስ የተባሉት ለአብነት እንደማቀርብ ቃል ገብቼ ነበር። ሶስቱን ባለፉት ተከታታይ ክፍሎች አቅርቤዓለሁ። ይህ ክፍል “ኢህአዴግን እርስ በርሱ ማናከስ” ላይ ያተኩራል።
መ. ኢህአዴግን እርስ በርሱ ማናከስ
ከታወቁ የጦርነት ስልቶች አንዱ ጠላትን ከፋፍሎ ማጥቃት ነው። ጠላት ከላይ ግዙፍና ጠንካራ ሊመስል ይችላል፤ ሆኖም መፍራት አያስፈልግም፤ ውስጡን በጥንቃቄ መመልከትና የተሰራባቸው ክፍልፋዮችን ለየብቻ ማጥናት ይገባል። ከዚያም ደካማዎቹን ክፍሎች በማጥቃት ጠንካራ የሚመስለውን ጠላት በቁርጭራጭ መጨረስ ይቻላል።
“የህወሓት አገዛዝ” ስንል ህወሓት ብቻ የሚገዛ ከመሰለን ትክክል አይደለም። እያንዳንዱ የኢህአዴግ ድርጅት ለየብቻ መጠናት ይኖርበታል። አራቱ፣ ማለትም ህወሓት፣ ብአዴን፣ ኦህዴግና ደህዴግ ቀዳሚ ትኩረት የሚሹ ናቸው። እንዲሁም አጋር ድርጅቶች የሚባሉት አብዴፓ፣ ቤጉህዴፓ፣ ጋህአዴን፣ ሀብሊና ኢሶዴፓ እያንዳንዳቸው በተናጠል ሊጠኑ ይገባል።
በዚህ ተከታታይ ጽሁፍ ክፍሉ ሶስት ላይ አንድ አስተያየት ሰጪ ተረብ በሚመስል መንገድ “እያንዳንዱ ነፃነት ናፋቂ ኢትዮጵያዊ” ማለት ምን ማለት ነው ሲል ጠይቆ ነበር። እነሆ እመልሳለሁ፤ “እያንዳንዱ ነፃነት ናፋቂ ኢትዮጵያዊ” ማለት ከህወሓት ዘረኛና ፋሺስታዊ አገዛዝ ነፃ መውጣት የሚናፍቅ ኢትዮጵያዊ ማለት ነው።
በህወሓት አገዛዝ የተማረርነው ከኢህአዴግ ውጭ ያለነው ኢትዮጵያዊያን ብቻ አይደለንም። ከህወሓት አገዛዝ ነፃ መውጣትን የሚናፍቁ ዜጎች ኦህዴድ፣ ብአዴንና ደህዴድ ውስጥ አሉ። ከህወሓት አገዛዝ ነፃ መውጣትን የሚናፍቁ ዜጎች አብዴፓ፣ ቤጉህዴፓ፣ ጋህአዴን፣ ሀብሊና ኢሶዴፓ ውስጥ አሉ። ከህወሓት አገዛዝ ነፃ መውጣትን የሚናፍቁ ዜጎች ህወሓትም ውስጥ አሉ። ይህን ስል እነዚህ ድርጅቶች ህወሓት የፈጠራቸው ባሮች ስብስቦች መሆናቸውን ዘንግቼ አይደለም።