Thursday, June 29, 2017

(የአርበኞች ግንት 7 ድምፅ ሬዲዮ)


አገዛዙ ሰሞኑን በአማራዉ ከልል በተለይም በጎንደር የሕዝቡን መሳሪያ ለማስፈታት አቅድ አዉጥቶ አየተንቀሳቀሰ መሆኑ ታወቀ፡፡ ለዚህም ማስፈጸሚያ ይሆን ዘንድ በአሁኑ ሰዓት ቁጥሩ አጅግ ብዙ የሆነ የአጋዚ ጦር በወረታ ከተማ፥ በአዘዞ በዳባትና በእብናት ሰፍሮ እንደሚገኝ ታውቋል ። ይህ አምባገነን ቡድን ከመነሻዉ የአማራን ሕዝብ አንደኛ ጠላት አድርጎ ከምድረ ገፅ ለማጥፋት ያልፈነቀለዉ ድንጋይ የለም፥ በህዝባዊ እንቢተኝነት ላይ ከፍተኛ ሚናን ይጫወቱ የነበሩ ኮረኔል ደመቀ ዘውዱን ቸምሮ ብርቅዬ ወንድሞቻችንና አህቶቻችንን ያለፍርድ በአስርቤት አያማቀቀ ይገኛል፡፡ አሁን ሕዝባችን መሳሪያዉን ከፈታ የመጨረሻ የባርነት ቀንበር አንደሚጣልበት ጥርጥር የለዉም ፥ በመሆኑም በሰሜኑ የኢትዮጵያ ክፍል የምትገኙ መሳሪያ ያላችሁ ወገኖች በሙሉ በእየ አካባቢያችሁ ታጥቀዉ አየተፋለሙ ከሚገኑት አርበኞች ጋር አየተቀላቀላችሁ የነጻነት ትግላችሁን አንድታፋፍሙ ጥሪ ቀርቦላችኋል፥ የአገዛዙ ቅጥረኛ ወታደሮች መሳሪያ ለመንጠቅ የሚጠቀሙበት ዘዴ በገበያ ቀናት ወይም በባዕላት ቀን በቀብር ስነስርዓት ላይ እንዲሁም በተለያዩ ምክንያቶች ቤት ለመፈተሽ በመሞከር ለምሳሌ፡- ሽፍታ ቤታችሁ ወይም አካባያችሁ ተደብቋል በማለትና በወንጀል ተጠርጥራችኋል እንዲሁም ቤት ውስጥ አባወራ የለም ብለው ባሰቡበት ጊዜ ወደ ሰው ቤት በመሄድ በህገወጥ መንገድ የቤት ፍተሻ በማድረግ መሳሪያ አላቸው ብለው የሚያስቡትን ሰው መሳሪያ ለማስፈታት ሙከራ እያደረጉ መሆኑ ስለተደረሰበት ህብረተሰቡ ከዚህ እራሱን እንዲከላከልና ትግሉን እንዲቀላቀል ጥሪ ቀርቧል፡፡

No comments:

Post a Comment