Wednesday, June 21, 2017

ኦህዴድ ውስጥ ከፍተኛ ውጥረት ሰፍኗል!!!

(የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ ሬዲዮ)

በኦህዴድ ውስጥ ያሉ የህወሓት ታማኞች ሌሎች የኦህዴድ አባላትን ማሳደድና ማሰር ጀምረዋል። 
በኦህዴድ ውሰጥ ያሉ ታማኝ የህወሓት አገልጋዮቸ አንፃራዊ በሆነ መንገድ የራስ መተማመንን በማዳበር ላይ ያሉትን የኦህዴድ አመራር አባላትን ማደን ጀምረዋል። ኦህዴድ ውስጥ ሆነው ህገመንግሥቱን በኃይል ለማፍረስ ተንቀሳቅሰዋል ሲሉ ከሰዋቸዋል። ባለፉት 2 ቀናት የምስራቅ ሸዋና የአርሲ 3 የዞን አመራሮች ታሰረዋል፡፡ ይህን ተከትሎ በተለያየ ደረጃ የሚገኙ 5 የኦሮሚያ ክልል ባለስልጣናት አገር ጥለው ወጥተዋል። በተመሳሳይ በርካታ በኦሮሚያ የሚገኙ የዞን አመራሮች መኖሪያ ቤት በደህንነቶች ድንገተኛ ፍተሻ ተደርጓል። ከዚህ ጋር ተያይዞ ከመሣሪያ ግምጃ ቤት 78 ክላሽ መሳሪያ መጥፋቱ እየተነገረ ይገኛል። በዚህም ምከንያት ኦህዴድ ውስጥ ከፍተኛ ውጥረት ሰፍኗል። ኦህዴድ ስልጠና በሚል ሰበብ ሃሙስ እለት ካድሬዎችን ለስብሰባ የጠራ መሆኑ ታውቋል።
ዝርዘር መረጃዎች እንደደረሱን እናቀርባለን

No comments:

Post a Comment