Wednesday, January 31, 2018

"እኛ ካልገዛናችሁ እንገነጠላለን" "እኛ ካልገዛናችሁ ሀገር ትፈርሳለች " ------------------------------ የሰው ልጅ በጥይት እንደ ቅጠል እየረገፈ ስለቁሳቁስ እና ንብረት መውደም ሲጨነቁ የከረሙት ህወሓቶች ለ26 ዓመታት ለመከፋፈያና ለማስፈራሪያ ሲጠቀሙበት የነበረውን አንቀጽ 39ን አቧራውን አራግፈው ስለመገንጠል እያቀነቀኑ ነው። ይህ የፕሮፓጋንዳ አካሄድ ከምን የመነጨ ነው? በርግጥ ህወሓት የትግራይ ሕዝብ ውክልና አለውን? በፕሮፓጋንዳ አፈቀላጤዎቹ ማህበራዊ ገጽ ላይ እየሄዱ መልስ መስጠቱና መከራከሩ ለተቃዋሚው ፋይዳ አለው ወይ? የሚዲያ ጥናት ባለሞያው ጋዜጠኛ እንዳልካቸው ኃይልሚካኤል የህወሓት ስልጣንና ጥቅም ከሌለ ኢትዮጲያ ትፍረስ የሚለው አስተሳሰብ በምርጫ 97 ወቅት ከሟቹ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ጀምሮ የነበረ እንደሆነ ይገልጻል። ሕዝቡ እንደቀደሞው ሁለተኛ ዜጋ ሆኖ ለህወሓት ተንበርክኮ የሚኖርበት ዘመን አብቅቶ ኢፍትሐዊነትን እየታገለ በመሆኑ በደኸው ላይ ተንደላቀው የሚኖሩ የስርዓቱ ተጠቃሚዎች ደንግጠው በቅዠት እየለፈለፉ ነው። የዛሬው ዛሬ ዝግጅት በዚህ ላይ ያተኩራል።

No comments:

Post a Comment