Wednesday, January 3, 2018

ህወሓት መቼም አይለውጥም:: መለወጥ ያለባቸው ተቃዋሚዎች ናቸው:: =========================================== *ኢህአዴግ ለሕዝባዊ ተቃውሞ የሰጣቸው መልሶች -በ2008 የመልካም አስተዳደር ችግር አለብኝ ግን ፀረ ሠላም ኃይሎች፣ሻዕቢያ፣ግንቦት 7... -በ2009 ጥልቅ ተሀድሶ ያስፈልገኛል ግን ፀረ ሠላም ኃይሎች፣ሻዕቢያ፣ግንቦት 7... -በ2010 አገሪቱ በፈፀምናቸው ስህተቶችና ከእድገታችን ጋር ተያይዘው በተከሰቱ አዳዲስ ለውጦችና ፍላጎቶች ምክንያት ለጊዜውም ቢሆን በአሳሳቢ ወቅታዊ ችግሮች ተወጥራ የቆየችበት ሁኔታ መፈጠሩን ገምግሚያለሁ። ግን ሕዝበኝነት... አዎ ህወሓት-ኢህአዴግ ቢገድልም፣ ቢያስርም፣ ቢያሰድድም፣ ስራ አጥነት ቢበዛም፣ ሕዝቡ ቢማረርም፣ መማመርር ብቻ ሳይሆን ለተቃውሞ አደባባይ ቢወጣም ስልጣኔን አልለቅም ብሎ ማሰር፣ማሳደድና መግደሉን ቀጥሎበታል። ይህ ለዶከተር ሰማኸኝ የሚደንቅ ጉዳይ አይደለም። "ህወሓት ለአራት አስርት ዓመታት የያየዘው ርዕዮተ ዓለም እንዲለወጥ አይፈቅድለትም። የህልውናው መሠረት በዚህ መልኩ መግዛት ነው" በማለት ዶክተር ሰማኸኝ ጋሹ ይተነትናሉ

No comments:

Post a Comment