Thursday, January 25, 2018

ትግሉ ከተጠቂነት ወደ አጥቂነት መሸጋገር አለበት !!

በወልዲያ ፣ ትላንትና ዛሬ ደግሞ በቆቦ የወያኔ ፋሽስቶች በህዝባችን ላይ እያደረጉ ያለው ዘግናኝ ጭፍጨፋ ይህ ወራሪና ቅኝ ገዢ መስል ኣረመኔ የጥቁር ሙሶሊኒዎች አገዛዝ ፈጽሞ የፓሊሲም የባህሪም ለወጥ ማድረግ የማይችል መሆኑን ያረገጋገጠበት ነው።
ከእባብ የእርግብ እንቁላል እንደማይጠበቅ ከወያኔ ስርአት የሚመጣ አንዳችም ለውጥ አይኖርም!
የኢትዮጵያ ሕዝብ የጀመረውን የነጻነት ትግል ማቀጣጠል ጊዜው አሁን ነው! በየአካባቢው ተደራጅቶ በመረጃና በጥናት ወያኔን መምታት አለበት። 
ትግሉ ከተጠቂነት ወደ አጥቂነት መሸጋገር አለበት! የወያኔ ፋሽስቶች ወጣት ሴት አዛውንት እየገደሉ የኢትዮጵያ ህዝብ ዘላለም ተጠቂ፣ ተበዳይ፣ ተረጋጭ፣ ተዋራጅ፣ ሆኖ ፈጽሞ መቀጠል የለበትም። 
ይህን ጨካኝ አረመኔ ጸረ ህዝብ ወራሪ ቡድን ራሱ የሚደማ፣ የሚሞት፣ ሊወድም የሚችል መሆኑን በተግባር ማሳየት፣ ማረጋገጥም ያስፈልጋል።

በሁሉም የኢትዩጵያ አካባቢዎች ይህን በተግባር መፈጸም በጥቂቶቹ ፋስቶች ጎራ ብርክን የሚያስፈን ነው ብሎም ስርአቱን ገዝግዞ የሚያወድም መሆኑን መጠራጠር የለብንም። 
ሁሉንም ቦታ ሊሽፍኑ አይችሉም ሃይላቸው እንዲበታተን በሁሉም አካባቢ ትግሉ መጠመድ፣ ወያኔም መመታት መድማት አለበት!

ሰለዚህ ኢትዮጵያዊ ሁሉ ይደራጅ፣ ይተባበር፣ ይታጠቅ ራስንና ወገኖችን ከወያኔ አረመኔ ነፈሰ ገዳዮች ይከላከል።
ወያኔንና ንብረቶቹን ማወደም ፣ ማዳክም፣ መቦርቦር የስረአቱን ውደቀት የሚያፋጥን የነጻነት ጎህ የሚቀድ ይሆናል!!
እንደራጅ! እናደራጅ! መደራጀት ! ተደራጅቶም ወያኔ በየአካባቢው ማዋከብ፣ መወጠር ወቅቱ አሁን ነው !!ጊዜው አሁን ነው!!
ከተጠቂነት ወደ አጥቂነት መሸጋገሪያው ጊዜ አሁን ነው!!
እያንዳንዱ ይህን መልክት በአገኘው መስመር ለህዝባችን ያስተላልፍ ! ያደራጅ ! አርበኞች ግንቦት 7 በሁሉም አካባቢዎች የህዝቡን ትግል የሚያጠናክሩ አርምጃዎችን ይወስዳል።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ መሆኑ አይቀሬ ነው!!
Image may contain: text

No comments:

Post a Comment