Thursday, April 26, 2018

ሰበር_ዜና ዘመቻ_ነበሮ" ዘመቻ ገዛኸኝ ነብሮ " በሚል ስም በተሰየመ ዘመቻ የአግ7 አርበኞች የህወሓት ወታደራዊ ካምፕ ላይ ጥቃት ፈፀሙ!


ሚያዚያ 17 ቀን 2010 ዓም ከምሽቱ 4:25 ሲሆን የአግ7 አርበኞች በጎንደር ከተማ አዘዞ የሚገኘውን የህወሓት ወታደራዊ ካምፕ ላይ ጥቃት የፈፀሙ ሲሆን በዚህ ጥቃት በርካታ የህወሓት ወታደሮች ጉዳት ደርሶባቸዋል፡፡

የተኩስ ልውውጡ ከምሽቱ 4:20 እስከ ለሊት 7:40 ማለትም ለ 3:20 ያክል የቆየ ሲሆን በካምፑ የሚገኙ 3 በሮች ማለትም ወደ ጎንደር አዘዞ ድልድይ ወደ ጭልጋ አዲሱ አውቶብስ ማረፊያ እና ከላይ ወደ ሎዛ ማሪያም በኩል ባሉ 3 የጥበቃ ክፍሎች ላይ ጉዳት ደርሷል፡፡ በዚህ ካምፕ የህወሓት የምዕራብ ዕዝ 42ኛ ክፍለጦር መገኛ ሲሆን የአዛዡ ጄኔራል ሲሳይ ጥበቃ ክፍልም ጉዳት ደርሶበታል፡፡ ይህ "ዘመቻ ነብሮ" ታቅዶበትና ልዩ ዝግጅት ተደርጎበት በተለይም "የአርበኛን ደም አርበኛ ነው የሚመልሰው" በማለት አርበኛ ገዛኽኝ ገብረመስቀል (ነብሮ) ከተሰዋበት ቀን ጀምሮ በሰሜን ጎንደር ቀጠና የሚንቀሳቀሱ የአግ7 አርበኞች በዚህ ጀግና ስም አንድ የተመረጠ ዘመቻ ለማካሔድ በመነጋገር የተሰራ አኩሪ ስራ ነው፡፡ አሁን እየደረሰን ባለው መረጃ የተኩስ ልውውጡ በምሽት በመሆኑ የደረሰው ጉዳት ከፍተኛ ሊሆን እንደሚችል ቢገመትም በወቅቱ 2 አንቡላንሶች የሞቱ እና የቆሰሉ ወታደሮቹን እያነሱ እንደነበር የአይን እማኞች አረጋግጠዋል በነበረው ውጊያ በአይን የታዩ የሞቱ የህወሓት ወታደሮች 13 ሲሆኑ ቆስለው ጎንደር ሆስፒታል የገቡ ደግሞ 9 ናቸው፡፡ በዚህ የተኩስ ልውውጥ የፍንዳታ እና ከፍተኛ ድምፅ ይሰማ እንደነበር እንዲሁም ከካምፑ ውስጥ አንድ ክፍል በፍንዳታው እንደፈረሰ የአይን እማኞች ገልፀዋል፡፡ ይህን ዘመቻ የተሳተፉ የቁርጥ ቀን ጀግኖች በሰላም ወደ ቀጠናቸው ተመልሰዋል፡፡ "አርበኛ ቢሰዋም እሱ የተሰዋለትን ዓላማ ከግብ የማድረሱ ትግል ይቀጥላል" በሚል መርህ ተከታታይ ድሎች ይኖራሉ፡፡ በአካባቢው ያለውን ዝርዝር ሁኔታ እየተከታተልን እናሳውቃለን፡፡ ድል ለሕዝብ !! የአግ7 ዘመቻ ነፃ ትውልድ፡፡

No comments:

Post a Comment