Sunday, July 5, 2015

ወያኔ አርበኞች ግንቦት 7 የከፈተበትን ጦርነት ከህዝብ ለመደበቅ እየሞከረ ነው

ወያኔ አርበኞች ግንቦት 7 የከፈተበትን ጦርነት ከህዝብ ለመደበቅ እየሞከረ ነው

July 5, 2015
ባለፉት ሦስት ቀናት የአርበኞች ግንቦት 7 ታጋዮች ትግራይ ውስጥ በተለያዩ ቦታዎች የወያኔን ሃይል ገጥመው የወያኔ መኮንኖችን ጨምሮ በርካታ የወያኔ ሰራዊት አባላትን እንደገደሉ በቃል-አቀባያቸው አማካኝነት ለኢሳት ቴሌቪዥን ገልጸዋል። ለጥቀውም እስከ ትላንት ድረስ ውጊያው ቀጥሎ እንደሚገኝ በድጋሜ ዜናውን አብስረዋል።
arbegnoch-ginbot7-fighters
በወያኔ ዘረኛና ግፈኛ አገዛዝ የተንገፈገፈው የኢትዮጵያ ህዝብም ጆሮውን አቅንቶ ሁኔታውን በመከታተል ላይ ነው። ቀድሞውንም የወያኔ ሥርዓት ያለ ሃይል ትግል አይንበረከክም፣ ኢትዮጵያ ውስጥ የፖለቲካም ሆነ የሥርዓት ለውጥ ሊመጣ የሚችለው በተቃውሞው ጎራ የተሰለፉት ተባብረው በወያኔ ላይ ክንዳቸውን ሲያሳርፉ ብቻ ነው ብለው የሚያምኑት ኢትዮጵያውያን አርበኞች ግንቦት 7 በወያኔ ላይ የከፈተውን ማጥቃት በከፍተኛ ደስታ ነው የተቀበሉት።
አንዳንዶች አርበኛውን በገንዘብ ለመደገፍ እና ለማጠናከር ከወዲሁ እንቅስቃሴ ጀምረዋል።

ይህ በዚህ እንዳለ በወያኔ ጎራ በኩል ይህን ጉዳይ በተመለከተ ምንም የተሰማ ነገር የለም። ጥያቄው… ለወትሮው ትንሽ ትልቁን “የግንቦት 7” አባል ነው ብሎ በመፈረጅ ንጹሃንን እስርቤት የሚወረውረው ወያኔ በይፋ ስለተከፈተበት ጦርነት ለምን ዝምታን መረጠ? ነው።
ዘረኛውና አምባገነኑ የወያኔ ሥርዓት ህዝብ እጅግ እንደጠላውና ሆ ብሎ ሊነሳበት እንዳቆበቆበ ይረዳል። ስለዚህም ጉዳዩ ከቁጥጥሩ ውጭ ሆኖ የህዝብ መነጋገሪያ እንዲሆን አይፈልግም። ያ ሆነ ማለት የተዳፈነው ፍም እሳት ፊቱ ላይ ተረጨ ማለት ነው።
ለዚህም ይመስላል በአርበኞች ግንቦት 7 የተሰነዘረበትን ጥቃት ለማብረድ ድምጹን አጥፍቶ መውተርተርን የመረጠው።
ሌላው ተጨማሪ ማስረጃ ደግሞ ወያኔ በአርበኞች ግንቦት 7 የተሰነዘረበትን ጥቃት ለመመከት ወደ አካባቢው እያሰማራ ያለው የጦር ክፍል ከአንድ ጎሳ የውጡና ቀደም ሲል በጡረታ ተሰናብተው ወያኔ ከወልቃይት ህዝብ ላይ ነጥቆ በሰጣቸው ለም መሬቶች ላይ የግብርና ስራ እያካሄዱ የሚገኙ የቀድሞ የህወሃት አባላት መሆናቸው ነው።

No comments:

Post a Comment