Sunday, July 16, 2017

የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ ሬዲዮ


የአርበኞች ግንቦት 7 ሰራዊት በሁለት የሰሜን ጎንደር ከተሞች የተሳካ ዘመቻ አደረገ። 
በሰሜን ጎንደር ዞን ችንፋዝ ስላሬ በተባለ ከተማ እና በበለሳ ጉሃላ ከተማ ከሀምሌ 6 ቀን 2009ዓም እስከ ሀምሌ 8 ለ9 ለሊት 2009ዓ/ም ድረስ በተጠቀሱት ሁለት ከተሞች ላይ በስርአቱ ሹማንቶችና የስርአቱ ቅጥረኛ ወታደሮች ላይ ጥቃት ተሰንዝሯል፡፡ 
በመሆኑም በስላሬ ከተማ በአንድ ቀን ውጊያ የስርዓቱ ወታደሮች እና መዋቅሩ ላይ ጉዳት በማድረስ ከተማውን መቆጣጠር የተቻለ ሲሆን በጉሃላ በግማሽ ቀን ውጊያ ከተማውን መያዝ ተችሏል፡፡ በጉሃላ የአስተዳዳሪው ጽ/ቤት እና የገቢዎች ጽ/ቤት በቦንብ የተመቱ ሲሆን። ለአጭር ጊዜ ከተማዋን የተቆጣጠሩት አርበኛ ታጋዮች በሰላም ወደ መጡበት ተመልሳዋል፡፡ በአሁኑ ስዓት አካባቢው ላይ ከፍተኛ ውጥረት ነግሷል፡፡ ታጣቂዎችም የገዢውን ሃይል በመክዳት ከነፃነት ኃይሎች ጋር በመቀላቀል ላይ ይገኛሉ።

No comments:

Post a Comment