Wednesday, July 26, 2017

ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ዛሬ ከሰጡት መግለጫ የተቀነጨበ: -



“የሕዝብ አመጽ በተደራጀ መንገድ እንዲካሄድና ለትግሉም የሚያስፈልገውን አቅርቦት በማዘጋጀት በኩል ለአመጽ ከተደራጀነው ኃይሎች የሚጠበቀውን ሁሉ እንደምናደርግና እያደረግንም እንደሆነ እንዲታወቅ እንፈልጋለን። የዚህ ዓይነቱ እንቅስቃሴ በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል ብቻ ሳይሆን በሁሉም የሀገራችን ክፍሎች እንዲስፋፋ ለማድረግ እየሠራንበት ያለው አብይ ሥራችን ነው። በዚህ መስክ የሚደረገው እንቅስቃሴ ዝግጅቱን በቶሎ አጠናቆ ሊደበቅ በማይችልበት ሁኔታ በግልጽ የሚወጣበት ግዜ ሩቅ እንዳልሆነ አረጋግጥላችኋለሁ። ይህ እንቅስቃሴ ብዙ ሕይወት ሳያስገብር ከዳር እንዲደርስ በወያኔ ስር ተጠርንፎ የሚገኘው የኢትዮጵያ ወታደር አሁንም በትንሽ በትንሹ እንደጀመረው በሰፊው ተንቀሳቅሶ ከሥርዓቱ ጋር ሳይሆን ከሕዝቡ ጎን እንዲቆም የምናደርገው ጥረትም ተጠናክሮ ይቀጥላል።”Image may contain: 1 person, closeup

No comments:

Post a Comment