Thursday, July 13, 2017

የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ ሬዲዮ


የአምቦ ከተማ ተቃውሞ እንደቀጠለ ነው፡፡
ለተቃውሞው ምክንያት የሆነው በቅርቡ ተገቢ ያልሆነ ግብር ነጋዴው ላይ መጨመሩ ሲሆን። ስርአቱ የህዝቡን ጥያቄ በሰላማዊ መንገድ ከመመለስ ይልቅ ሃይልን መፍትሄ አድርጎ መንቀሳቀሱ በተፈጠረው ግጭት አንድ የፌደራል ፓትሮል መኪና ሲቃጠል ሌላ ተሰባብሯል፡፡ እንዲሁም አንድ አውቶብስ ላይ የመሰባበር አደጋ ደርሶበታል፡፡ ከፍተኛ ተኩስ እንዳለና ወደ ወለጋ የሚወስደው መንገድም እስካሁን እንዳልተከፈተ ለማወቅ ተችሏል፡፡ በከተማው ያሉ አገልግሎት የሚሰጡ ተቋማት ሙሉ በሙሉ ተዘግተዋል። ከፍተኛ የግብር ጭማሪን ተከትሎ በሌሎች አካባቢዎች የተቃውሞ እንቅስቃሴ ሊኖር እንደሚችል አስተያየት ሰጪዎች ይናገራሉ

No comments:

Post a Comment