Wednesday, April 8, 2015

በደህንነት ቢሮ ውስጥ የተጀመረው ማጥራት ቀጥሏል::18 አባላቱ በቁጥጥር ስር ውለዋል:: April 8, 2015

በሕወሓት መሪነት የሚዘወረው የደህንነት ተቋሙ በኢሕበሕወሓት መሪነት የሚዘወረው የደህንነት ተቋሙ በኢሕአዴግ ውስጥ የዘለቀውን የመበስበስ አደጋ ተከትሎ በስልጣናችን ላይ ችግር ይፈጥራሉ ለድርጅቱ ሳይሆን ለሕዝብ እያደሉ ነው::ከተቃዋሚ ሃይላት መረጃ አምጡ ሲባሉ የሚዘናጉ እና አላስፈላጊ መረጃ ይሰጣሉ::ከአውሮፓ ዲፕሎማቶች ጋር ለምን አላማ እንደሆነ በማይታወቅ መልኩ ግንኙነት ፈጥረዋል ወዘተ ያላቸውን አስራ ስምንት አባላቱን በቁጥጥር ስር ማዋሉን ከደህንነት ቢሮ የተገኙ መረጃዎች ጠቁመዋል::

በሙስና እና የዘረፋ ቡድን በማሰማራት የሚታወቁት አቶ ጌታቸው አሰፋ የሚመሩት የደህንነት ተቋም በውስጡ የተነሳውን አለመተማመን ተከትሎ የጀመሩት አባላቱን እየመዘኑ ማጥራት እርምጃ ላይ የትግራይ ተወላጆች እና እርትራውያን የስለላ አባላት እንዳልተነኩ ሲታወቅ በአሁን ሰአት ከፍተኛ አትኩሮት የተደረገባቸው ኢትዮጵያውያን ላይ ቢሆንም ነገ እና ተነገወዲያ የትግራይ ተወላጆቹ እና ኤርትራውያኑ ላይ ቢላው ማረፉ እና በአዳዲስ መተካታቸው አይቀርም ተብሏል::የመጀመሪያ ዙር 3000 ሰልጣኞች ከሃገር ውስጥ እና ከዲያስፖራው ተወጣጥተው በተለያዩ የሃገሪት ክፍሎች ባሉት ማሰልጠኛ ጣቢያዎች የደህንነት ትምህርቶች እየተሰጧቸው ሲሆን እየተጣሩ ሊባረሩ የታቀዱትን የሚተኩ መሆናቸው ታውቋል::
በቁጥጥር ስር የዋሉት አስራ ስምንቱ የደህንነት አባላት በሆቴሎች እና በኤርፖት አከባቢ የሚሰሩ ሲሆን አብዛኛው ስራቸው ኤምባሲዎችን እና ኤንጂኦ ሰዎችን መሰለል እንዲሁም በየኤምባሲው እና የውጭ ድርጅቶች ውስጥ የሚሰሩ መረጃ አቀባይ ኢትዮጵያውያን ጋር የተቀናጀ ስራ መስራት ሲሆን ከሃገር ቤት የተቃዋሚ ሃይሎች የውጪ ግንኙነት ሕዋሶችንም የሚስልሉ የደህንነት አባላት በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ምንጮች ለምንሊክ ሳልሳዊ ገልጸዋል::ተጨማሪ መረጃዎች እና በቁጥጥር ስር የዋሉ የደህንነት አባላት ስም ዝርዝር በዚህ ሰሞን ይፋ ይደረጋል::አዴግ ውስጥ የዘለቀውን የመበስበስ አደጋ ተከትሎ በስልጣናችን ላይ ችግር ይፈጥራሉ ለድርጅቱ ሳይሆን ለሕዝብ እያደሉ ነው::ከተቃዋሚ ሃይላት መረጃ አምጡ ሲባሉ የሚዘናጉ እና አላስፈላጊ መረጃ ይሰጣሉ::ከአውሮፓ ዲፕሎማቶች ጋር ለምን አላማ እንደሆነ በማይታወቅ መልኩ ግንኙነት ፈጥረዋል ወዘተ ያላቸውን አስራ ስምንት አባላቱን በቁጥጥር ስር ማዋሉን ከደህንነት ቢሮ የተገኙ መረጃዎች ጠቁመዋል::
በሙስና እና የዘረፋ ቡድን በማሰማራት የሚታወቁት አቶ ጌታቸው አሰፋ የሚመሩት የደህንነት ተቋም በውስጡ የተነሳውን አለመተማመን ተከትሎ የጀመሩት አባላቱን እየመዘኑ ማጥራት እርምጃ ላይ የትግራይ ተወላጆች እና እርትራውያን የስለላ አባላት እንዳልተነኩ ሲታወቅ በአሁን ሰአት ከፍተኛ አትኩሮት የተደረገባቸው ኢትዮጵያውያን ላይ ቢሆንም ነገ እና ተነገወዲያ የትግራይ ተወላጆቹ እና ኤርትራውያኑ ላይ ቢላው ማረፉ እና በአዳዲስ መተካታቸው አይቀርም ተብሏል::የመጀመሪያ ዙር 3000 ሰልጣኞች ከሃገር ውስጥ እና ከዲያስፖራው ተወጣጥተው በተለያዩ የሃገሪት ክፍሎች ባሉት ማሰልጠኛ ጣቢያዎች የደህንነት ትምህርቶች እየተሰጧቸው ሲሆን እየተጣሩ ሊባረሩ የታቀዱትን የሚተኩ መሆናቸው ታውቋል::
በቁጥጥር ስር የዋሉት አስራ ስምንቱ የደህንነት አባላት በሆቴሎች እና በኤርፖት አከባቢ የሚሰሩ ሲሆን አብዛኛው ስራቸው ኤምባሲዎችን እና ኤንጂኦ ሰዎችን መሰለል እንዲሁም በየኤምባሲው እና የውጭ ድርጅቶች ውስጥ የሚሰሩ መረጃ አቀባይ ኢትዮጵያውያን ጋር የተቀናጀ ስራ መስራት ሲሆን ከሃገር ቤት የተቃዋሚ ሃይሎች የውጪ ግንኙነት ሕዋሶችንም የሚስልሉ የደህንነት አባላት በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ምንጮች ለምንሊክ ሳልሳዊ ገልጸዋል::ተጨማሪ መረጃዎች እና በቁጥጥር ስር የዋሉ የደህንነት አባላት ስም ዝርዝር በዚህ ሰሞን ይፋ ይደረጋል::

No comments:

Post a Comment