Sunday, April 5, 2015

ህወሃት መሪ ያጣ ድርጅት ነው። እኔ ለህወሃቶች የምመኝላቸው፣ እውነተኛ ራእይ ያለው መሪ እንዲያገኙ ነው።
ለነገ ሳይስቡ ዛሬ ሆድን በኪሳራ ከሞምላት፣ እራስን ከማወደስ፣ ሌሎችን ከማኮሰስ፣ አፈናቅሎ ከመውረስ፣ አምታቶ ከመዝረፍ፣ በሃሰት ከመክሰስ፣ ህዝብን ፈርቶ ከመኖር፣ በደካማ ዜጎች ስቃይ ከመደሰት፣ በዘርና በጎጥ ከመከፋፈል፣ በባዶው ከመጎረር፣ የሃሰት ክብርና ዲግሪ ከጥቁር ገበያ በርካሹ ከመሰብሰብ፣ ጥራት የሌላቸው የሰው አሻንጉሊቶች ከመሰብሰብ የሚያድን መሪ ያስፈልጋቸዋል።

ህወሃቶች ቆራጥ መሪ ሲያገኙ የትናንቱ ስህተታቸው ሁሉ ፍንትው ብሎ ይታያቸዋል። የበደሉትን ሁሉ ይቅርታ ይለምናሉ። አገር ማለት ሁሉም ያልአድርኦ በዜግነቱ ተከብሮ ከማንም ሳይበልጥ ከማንም ሳያንስ ሊኖርበት የሚገባ ምድር መሆኑ ይገለጥላቸዋል። ህወሃቶች መሪ ሲያገኙ ወደ ገደል ቁልቁል ከማብረር ይድናሉ። ፍሬን ይይዛሉ! ቆም ብለው ያስባሉ...
"ውድ የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ! በነጻነት ስም፣ ለችግር፣ ለመከራ፣ ለስደት፣ ለእስራት፣ ለግድያ፣ ለግፍ፣ ለዝርፊያ፣ ለአድልኦ፣ ለስርአት አልባነት፣ ተዘርዝሮ ለማያልቅ በደልና ግፍ ዳርገንሃል። ለሁላችንም የሚሆን አዲስ ምዕራፍ መክፈት ግድ ሆኖብናል። ይቅርታህን እንለምናለን!" የሚል ደፋር መሪ ያሳፈልጋቸዋል። የኢትዮጵያ ህዝብ ሁል ግዜም ይቅር ባይ ነው።
መንደር መሃል እንደነጋበት ጅብ መሄጃ ከማጣቱ በፊት ህወሃት ደፋር መሪ እንዲኖረው እመኝለታለሁ። የእነ መለስን ስህተት ከሚደግም መሪ ይልቅ እወነተኛ ራእይ ያለው ቆራጥ መሪ ያስፈልገዋል። አርቆ አሳቢ፣ ከአድልኦ እና ጠባብነት የጸዳ ከዛሬ ከንቱነት ይልቅ ለመጪው ትውልድ ሁሉ የሚያስብ መሪ...

No comments:

Post a Comment