Friday, November 17, 2017

የአርበኞች ግንቦት 7 ታጋዬች የህወሐት ወታደራዊ ካምፕ ውስጥ ሰርገው በመግባት ጥቃት ፈፀሙ፡፡ (የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ ሬዲዮ)

ህዳር 7 ቀን 2010 ዓ/ም ንጋት 10:55 ሲሆን ጎንደር አዘዞ ወታደራዊ ካምፕ በአርበኞች ግንቦት 7 ታጋዮች ጥቃት ተፈፀመበት ፡፡ ከመስከረም ወር 2010 ዓ/ም ጀምሮ ካምፑን ቀደም ሲል ከነበረው 24ኛ ክፍለ ጦር የተረከበው የ42ተኛ ክፍለ ጦር የጦር መጋዝን ንጋት ላይ እጅግ ጥንቃቄ በተሞላበት መልኩ በተፈፀመው ጥቃት መጋዝኑ በከፊል የተቃጠለ መሆኑ ታውቋል፡፡ ከዚያም የአየር መንገድ እና የጎንደር ከተማ እሳት አደጋ ደርሰው በከፍተኛ ርብርብ ሙሉ በሙሉ ከመቃጠል ሊድን ችላል ፡ ይህ ጥቃት ህዳር 6 ቀን 2010 ዓ.ም. ምሽት ከካርቱም ወደ መቀሌ ነዳጅ ጭኖ ሲመጣ በነበረው ተሽከርካሪ ላይ ጥቃት የተፈፀመ ሲሆን ይሄን ጥቃት በፈፀሙ ታጋዮች ላይ ለክትትል ወታደሮች ሲወጡ ነው የጦር መጋዝኑ ላይ ጥቃት የተፈፀመው ፡ ከጥቃቱ ጋር በተያያዘ ተረኛ መኮነን የነበረው ምክትል መቶ አለቃ ደረጄ ጉደታ እና የበር ዘብ የነበረው ምክትል አስር አለቃ የኔሁን ጥላዬ በቁጥጥር ስር ውለው ሲታሰሩ በካምፑ ጭልጋ በር በተባለ ማማ ላይ የነበሩ ሁለት ወታደሮች ከነ ሙሉ ትጥቃቸው ተሰውረዋል፡፡
ምስል ከፋይል
Bilderesultat for አርበኞች ግንቦት 7

No comments:

Post a Comment