Sunday, November 12, 2017

የኢሳት 7 ኛ ዓመት ትናንት ቅዳሜ በአምስተርዳር በልዩና በደማቅ ሁኔታ ተከብሯል። በአምስተርዳም የኦሮሞ ኮሙኒቲ አባላት ለበዓሉ ድምቀት ላሳያችሁት አስገራሚ ተሳትፎ ምስጋናችን ታላቅ ነው።

"ኢትዮጵያ የኛም ሀገር ናት፣ ኢሳት የኛም ነው" በማለት በዝግጅቱ ቦታ በመገኘታችሁ " ኢትዮጵያ ሀገሬ፣መመኪያ ጋሻዬ" በሚለው ሙዚቃ መድረክ ላይ ተጋብዛችሁ በልዩ ደስታ የተጫወታችሁ የጅቡቲ ሶማሌዎች ለእናንተም ምስጋናችን ይድረሳችሁ። ከሁሉም በላይ የመድረኩ ፈርጥና ድምቀት ለነበራችሁት ለአርቲስት ሃኒሻ ሰሎሞንና ለአርቲስት ቱሉ ምስጋናችን ወደር የለውም።
በመጨረሻም የአምስተርዳምና አጠቃላይ የሆላንድ የኢሳት ድጋፍ አስተባባሪ ኮሚቴዎች፣ የሥራችሁን ስኬት አምሮ ስላገኛችሁት እንኳን ደስ ያላችሁ፣
Image may contain: 7 people, people smiling, people standing and suit
Image may contain: 3 people, people smiling

No comments:

Post a Comment