Friday, January 2, 2015

ምክትል መቶ አለቃ ተስፋየ ገብረአብ እንዴ Theodor Fritsh,
የምክትል መቶ አለቃ ተስፋየ ገብረአብ ሰሞኑን ከመቸዉም ጊዜ በበለጠ ተከታዮቹንና አድናቂወቹን ኦሮሞዎች የሚያሸማቅቅና የሚያሳፍር የእራሱንም ድንቁርና የሚያሳብቅ የቅዳሜ ወግ በሚለዉ ገጹ አንድ ጽኁፍ አዉጥቶል ፤፤ የኦሮሞ ህዝብ እስከመቸ በዚህ እኩይ በስሙ እየተነገደበት እንደሚኖር አይገባኝም ፤፤ጭራሽ ይሄን ሰዉ ተከታዮቹ ገዳ የሚል ስም መርቀዉለት እሱም እነሱን ወክሎና ሆኖ መርዙን እየረጨ ይገኛል፤፤
መቶ አለቃ ተስፋየ ገብርአብ በእናቱም በአባቱም ኤርትራዊ ሲሆን ተወልዶ ያደገዉ ደብረዘይት ነዉ፤፤በደርግ ዘመን ወታደር የመሆን ፍላጎት የተነሳ የመቶ አለቅነት ኮርስ ወስዶ በምክትል መቶ አለቅነት ከተመረቀ በሆላ በደርግ በኩል ተሰለፎ ጎንደር ደብረታቦር ግንባር ከወያኔ ጋር ሲዋጋ አንድት ጥይት ሳይተኩስ ለወያኔ- ሻአቢያ እጁን እንደሰጠ ይታወቃል፤፤ ሁሌም የተስፋየ ገብር አብ ገጸ ባህርያት ተጨዋቾች በብሄርና በብሄረሰብ አጋ ለይተዉ እንጨፋጨፍ እንሰያየፍ የሚሉ ናቸዉ፤፤
ዛሬ ደሞ ተስፋየ ገብርአብ የነሞሶሎኖንና የሂትለርን የዘር ፖሊሲ ነፍስ ዘርቶ ለኦሮሞ ህዝብ ምክሩን እየለገሰ ነዉ ፤፤ እዉነተኛ የፍቅር ታሪክ ባለዉ ጽሁፉ ማንኛዉም ኦሮሞ ከሌላ ጋር መጋባት ወይም መዋለድ የለበትም ይላል ፤፤በተለይ የተስፋየ ገጸ ባህሪያት አንድ ኦሮሞ ወንድና አንድት የአማራ ልጃገረድ ናቸዉ፤፤ በዚህም ከፍተኛ የሆነ ድንቁርና በሚያሳብቅበት ጽሁፉ ‹‹ብዙ አማሮች ግማሽ ኦሮሞ አለብን ማለት ያዘወትራሉ ፤፤በተቃራኒዉ ግን ኦሮሞወች ይሄን ሲሉ አይስተዋልም ›› እያለ ለመሳለቅ ይሞክራል ፤፤
የተስፋየ ገብረ አብ ጽሁፍ ማጠንጠኛዉ ንጹህ የሆነ ደም ያለዉ ኦሮሞ መፍጠር ነዉ ፤፤ነገር ግን ይሄን ንጹህ ኦሮሞ የመፍጠር ፕሮጀክቱን ተግባራዊ የሚያደርግበት ቦታ መፈለግ ያለበት ይመስለኛል ምናልባት እስካሁን ሰዉ ያልሰፈረበት ደሴት ፈልጎ ንጹህ እና ምንም ቅልቅል የሌለባቸዉን ኦሮሞ ተወላጆች ፈልጎ በላቦራቶሪ በታገዘ ምርምር እንደነ ሂትለር ተግባራዊ እናድርግ ሳይል አይቀርም ፤፤ ለዚህም እኩይ ፕሮጀክቱ ደናቁርት ተከታዮችእንደማያጣ እሙን ነዉ፤፤ ተከታይ ቢኖረዉም አይደል እቅፍ ድግፍ አድርገዉ የዳቦ ስም ሰጥተዉ ልጃችን ነህ እያሉ በመርዝ አቡክቶ የጠፈጠፈላቸዉ ቂጣ የሚጎምዱት ፤፤
ይሄ የሚያሳየዉ ይሄን የነሂትለር እና የሞሶሎኒን የዘር ፖሊሲ የወረሰዉ ሹምባሻ እና ባንዳ ከነበሩት ቅድመ አያቶቹ መሆኑ አይካድም ምክንያቱም የሙሶሎኒዋ ኢጣልያ በኤርትራ ላይና በተወሰነ የኢትዮጵያ ክፍል አሁን ተስፋየ እየሰበከ የነበረዉን የዘር ፖለሲሲ ተግባራዊ ሲያደርጉት እንደነበር አልቤርቶ ሰባኪ እንደዚህ ይነግረናል
“የኢጣልያ የዘር ፖሊሲ አንዱ ትዳር የሌላቸዉ ኢጣልያኖች ኤርትራዉያን የቤት ሰራተኛ እንዳይኖራቸዉ ሲከለከል ፤፤ አንዱ የዚህ የዘር ፖሊሲ መለያ በ1937 የወጣዉ የዘር ቅልቅል ጋበቻን የሚያስቀረዉ ህግ ነዉ፤፤ለምሳሌ በሰኔ ወር 1939 አም ህግ የኢጣልያንን ዘር የሚያዋርድ ተግባር ሲፈጽም በተገኘ ኢጣልያዊ ላይ ከባድ ቅጣት ተወስኖበታል፤፤
የዚህ ህግ ቅጽበታዊ ዉጢትም የኢጣልያ ዉስጥ ካገሬዉ ተወላጅ የተጋቡ የኢጣልያ ዜጎች በዘዴ እንድፋቱ የሚያደርግና ለብዙ አመታት በህጋዊ ጋብቻ ተሳስረዉ የኖሩ ቤተሰቦችን መበታተን ነበር ፤፤ ይሄንም ለመካላከል ሲባል የኢጣልያ መንግስት ማዳም ሚራ የሚባሉ ኢጣልያዊት ሴተኛ አዳሪ የሆኑ አሻሻጮቾ ጋር እንድትመጣ ታዛ ነበር ፤፤
ሌላዉ ሙሶሎኒ ከኢጣልያ ወንዶችና ከኢትዮጵያዉያን ሴቶች ሞቃድሾ ዉስጥ ህጻናት ማሳደጊያ አቆቆቀሞ ያሳድጋቸዉ ነበር በኤርትራም ከሁለቱ ዘሮች የተወለዱ ህጻናት በካቶሊካዊዉ ቅዱስ ዮሴፍ ተቆም እንድያድጉ ተደርገዉ ነበር፤፤›› ይለናል ፤፤
በተጨማሪም ዶ/ር ሀይለማርያማ ላሬቦ ስለጀርመኑ ሂትለር ሲነግሩን ‹‹፣ ሂትለር የቆመው የራሱ ዘር ማለትም ጀርመን የሁሉንም ሰው ዘር ጨርሶ ፈጅቶ ሌላውን እንዲተካ ነው። ሂትለር በጀርመን ዘር አምባገንነት እንጂ በሰው ዘር እኩልነት ከቶውኑ አያምንም። የዓለምን ሕዝብ በተፋሰስ ደርድሮ ሲያበቃ፣ ጥቁሮቹን ያስቀመጠው ከሥሩ ዕርከን ነው። በሱ አስተሳሰብ፣ እልቂታቸዉም መፈጸም ያለበት ከሥር ካለው ጀምሮ ነው፣ ፤
ከዚህም አልፎ፣ በሂትለር ዘንድ ሁሉም ጀርመን የጠራ ስላልሆነና፣ የጀርመንን ሕዝብ ባሕርይ ስለማያንፀባርቅ፣ ጠንቀኞች ናቸው ያላቸዉን አካለ-ስንኩሎቸን፣ ደካሞችን፣ በሽተኞችንና፣ አጭሮችንም ጭምር ፈጅቷቸዋል። እነዚህ የፈረደባቸው የመጀመርያው ድርጎው ናቸው። ችግር ባይገጥመው ኖሮ፣ ተራው በሱ ዘንድ በደምብ ነጣ ባላሉት ጀርመኖች በሆነ። የዓለም መንግሥታት እንደነቁ፣ ተረባርበው የቀረዉን ሌላዉን እምነቱን እግብር ላይ ከማዋሉ በፊት አጠፉት እንጂ፣ ዝም ቢባልና ዕድሉ ቢገጥመው፣ በእምነቱ መሠረት ጥቁሮቹ መጀመርያዎቹ በሆኑ ነበር። ይሁንና መንግሥታቱ ሊያጠፉት የቻሉት፣ አጠገቡ የነበሩትን ስድስት ሚሊዮን አይሁዶችን በአሰቃቂ ሞት ከፈጀ በኋላ ነው።››
ከዚህ መረዳት የሚቻለዉ እንደተስፋየ ገብርአብ ያሉትና፡ በአገራችን በዘዉገኝነት ጽንፈኞች የሚመሩት የሂትለር እና የሞሶሎኒ አድናቂዎችም፣ መኖራቸዉን ነዉ፤፤ በኢትዮጵያ ውስጥ ባንዳንድ ብሔረ-ሰብ ላይ የፈጸሙት እልቂት፣ ልክ ይኸንኑ ኢሰብኣዊ ዐይነት ድርጊት ሳይተካከለው አይቀርም። ግን የአሁኑ የአገራችን ሰው ከመጮህና ከመለፍለፍ አልፎ በድርጊቱ መዘገነኑን በግብር ስለማያሳይ፣ ከእነዚህ አረመኔዎች አብዛኞቹ ካገር ቤት ወጥተው እንደሌላው ንጹሓን ስደተኞች መስለው፣ ማንም ሳይነካቸው፣ በምዕራብ አገር ተንደላቅቀውና ተንፈላስሰው እየኖሩ ናቸው።
ተስፋየ ገብርአብ ሲያስነጥሰው መሃረብ ይዘው በሚቀርቡ አጎብዳጆቹ አማካይነት የጥላቻ መርዛማ ቃላትን፣ የሚቆጠቁጡ ባዶ ዲስኮሮችን እና እርባናየለሽ ምዕናባዊ ስዕል በአዕምሮው ላይ እየፈጠረ አጼ ምኒልክ የግዛት ማስፋፋት ጥማታቸውን ለማርካት ሲሉ በዜጎች ላይ የጭካኔ ተግባራትን እንደፈጸሙ በማስመሰል ለምንም የማይጠቅሙ እርባናየለሽ እና ተራ አሉባልታዎችን በማሰራጨት ላይ ይገኛል፡፡ይህ በከፍተኛ ጥንቃቄና የሸር ጥልፍልፍ ወይም ሤራ (Conspiracy) የተስፋየ ገብርአብ የተጨፋጨፉ ዕቅድ ጅማሮው ቀደም ሲል በወያኔ አይዞህ ባይነት እና በእነ አቦይ ስብሀት አጋፋሪነት ነዉ፤፤ የታሪክ ማጠልሸት ዘመቻው በዋናነት እየተከናወነ ያለው ምኒልክን ማእከል በማድረግ ነዉ ፤፤
በመሰረቱ ታላቁና የዘመናዊ ኢትዮጵያ መሀንድስ የሆኑት ምኒሊክ የግዛት መስፋፋቱን ሲያደርግ በሁለት መንገድ እንደሆነ ግልጽ ነዉ ፤፤
1- በሰላማዊ መንገድ -
ይህ መንገድ ሁሌም ቢሆን ታላቁ ሚኒሊክ የሚመርጠዉና ብዙ የደቡብ፤ ደቡብ ምስራቅና ደቡብ ምእራብ አካባቢወች ወደ ማእከላዊ መንግስት ስር የተጠቃለሉበት ሂደት ነዉ፤፤ ሕዝብን በግድ ሳይሆን በፍቅርና በዘዴ መግዛት ሲሆን፣ ለዚህም በሕዝቡ ዘንድ እሱ የለመደውና የሚያውቀው ያገሩ ባላባት ተቀባይነት ይኖረዋል ብለው ስላመኑበት፣ የተማረከዉን ገዢ መልሰው በቦታው ይሾሙ ነበር። ካልሆነም ልጁን ወይንም ሕዝቡ ተሰብስቦ የመረጠውን ያስቀምጡ ነበር። ለምሳሌ እነዚህን አካባቢወች ብናይ ወለጋ ፤ ጅማ ፤ ባሌ፤ የተወሰነዉ የአርሲ ክፍል በተለይም የክርስትና እምነት ተከታዮች ያሉበት የአርሲ ክፍል በሰላም ነዉ የምኒልክን ንጉስነት አምነዉ በማእከላዊዉ መንግስት ስር ሲተዳደሩ የነበሩት ፤፤
በዚህም መሰረት በዚህ አካባቢ ይኖሩ የነበሩት ህዝቦችም ሆነ ፊዉዳሎች እንኮን ነፍጠኛ የሚባለዉን ነገር በሩቅ በስማበለዉ ካልሆነ በቀር የሚያዉቁት ነገር አልነበረም፤፤
እንደ ወለጋ ያሉት ግዛቶች ደሞ አቶ አሰፋ ጫቦ እንዳሉት ለምኒልክ አትልፋ ወርቁንም ሁሉንም ነገር ይዘን መጥትን እንገብራለን ነዉ ያሉት ፤፤ ነገር ግን አስቂኙ ነገር አክራሪዉንና ኦነግን መስርተዉ እና እየመሩ መጥተዉ ለብዙ ንጽሀን ደም ተጠያቂ የሆኑት የኦነግ መስራቾች ነፍጠኛን የማያዉቁትና አጼ ምኒልክን ሰራዊት ጸሀይ አይምታህ ግብርህን እዛዉ ድረስ ይዘን እንመጣለን ብለዉ ያሉት ናቸዉ፤፤
2- በጦር ሀይል -
አጼ ምኒሊክ መዋጋትንም ይመርጡት የነበረው ባላባቱ፣ በሰላም ግበር ብለው አስቀድመው ደጋግመው ለላኩት ጥሪ፣ አሻፈረኝ ሲላቸውና፣ ሌላ አማራጭ ሲያጡ ብቻ ነበር። ማንኛዉም የአለም ሀገር ታሪክ እንደሚያሳየን ማንኛዉም የዘመናዊ ሀገር ግንባታ አልጋ በአልጋ ሆኖ አያዉቅም በዚህ ሂደት ዉስጥ የተወሰነ ማህበረሰብ መጎዳቱ እሙን ነዉ ፤፤ በዚህም መሰርት በሰላማዊ መንገድ አርሲ ሀረር ወላይታ ጉራጌ አካባቢ ከፋ ሃድያ የመሳሰሉት ነበሩ፤፤ በነዚህ አካባቢ በወረራ የተከሰተን የሰዉ ጉዳት በጣም እያጋነኑ የፈጠራ ድሪቶ በመደረት ጥላቻን መንዛት ነዉ፤፤
እንግድህ ትንሽ ቆሎ ይዘህ ወደ አሻሮ ተጠጋ እንደሚባለዉ ተስፋየም አጼ ምኒሊክ በዘመናዊት ኢትዮጵያን የመገንባት ሂደት ወቅት የተከሰቱ ችግሮችን እያነሳ ኦሮሞ ከአማራ ጋር ፈጽሞ መጋባትም ሆነ መዛመድ የለበትም እያለ መርዙን እየረጨ ይገኛል፤፤ለተስፋየ ገብርአብን ደሞ መሎከታዊ ስብእና እንዳለዉ የሚያሸረድጉለትና አቅፈዉ ደግፈዉ እሹሩሩ የሚሉት ደሞ የአማራ ነፍጠኛ በምኒሊክ መሪነት እነተስፋየ ገብርአብ አማራ ህዝብ የኦሮሞ ህዝቦች ጠላት እንደሆኑ አድርገው ታሪክን በመበረዝ የታሪክ ድሪቶ አቀነባብረው እንደገና የጎደፈ ታሪክ ለመጻፍ ይታትራሉ፡፡የነተስፋየ ገብር አብ የፖለቲካ ባህላችንን ከምንጊዜውም በበለጠ ሰው-በላ እንድሆን ማድረግ ነዉ ። በማህበረሰባችንም ስነልቡና ላይ የእርስበርስ ጥርጣሬንና መፈራራትን እንድያድር ማድረግ ነዉ። ማህበራዊ ግኑኝነታችን በከፍተኛ ጥንቃቄና ጥርጣሬ የታጀበ እንዲሆን አድርጎአል። 

ህሊናቸው በዘርኝነት የሚመሩ እንደተስፋየ ያሉ መርዘኛወች ማንኛውንም ነገር በዘር ነክ ሁኔታ መናገር ማስፈፀም ያዘውትራሉ ፤፤ሌላውን ይንቃሉ፤፤ ሌት ተቀን ሌላውን ለማዳከም ብሎም ለማጥፋት ይሰራሉ ፤፤የሚያገኙትም ዉጤት ጥላቻን እና ቂምን ማስፋፋት ነው ይህ ደግሞ ለነሱ ምንም ጥቅም የለውም ጉዳት እንጂ የሚጠቀመው የዘርኝነት መንፈስ በሕሊናቸው ያለው ብቻ ነው፤፤ :ዘረኝነት ባመጠዉ በሺታ ዛሬ ዛሬ አንድ ትግሬ ሲሞት ወያኔ ነዉ እንኮንም ሞተ፤፤ አንድ አማራ ሲሞት ይበለው ደሞ ለነፍጠኛ ፤፤ አንድ ኦሮሞ ሲሞት ኦነግ ነዉ እንኮንም ሞተ ወዘተ.. ወደሚል ሰብዓዊ ፍጡራን መሆናችንን ወደሚያስረሳን ደረጃ አድርሶናል።
ፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም ስለዘረኝነትና ጥላቻ እነደሚከተለዉ ይሉናል፤ ጥላቻ የነብሳችን የመጨረሻው የበሽታ ምልክት ነው፡፡ ጥላቻ ኢምክንያታዊ ነው ወይም አመክንዮ የለውም፡፡ በጥላቻ ላይ የተጻፉ በርካታ ሳይንሳዊ ጽሁፎች እንደሚያመለክቱት በጥላቻ የተመረዙት ምንጊዜም ይጠላሉ ምክንያቱም ይፈራሉ፣ ደህንነት አይሰማቸውም፣ ምቀኞች ናቸው፣ ወይም ደግሞ እራሳቸውን ይጠላሉ ምክንያቱም የጥላቻቸው መነሻ እና መድረሻ እነዚሁ በጥላቻ የተሞሉት ግብዞች ናቸውና፡፡ ከሁሉም በላይ በጥላቻ የተሞሉት ወገኖች እራሳቸውን ይጠላሉ ምክንያቱም ብቁነት የጎደላቸው፣ ኃይልየለሽነት፣ ተስፋቢስነት፣ እና የእረዳትየለሽነት ስሜት የተጠናወታቸው ነው፡፡
ማንዴላ እንዲህ ብለው ነበር፣ “ሰው በቆዳው ቀለም፣ ወይም ደግሞ በማንነቱ፣ ወይም በኃይማኖቱ ምክንያት ብቻ ማንም ማንንም ሊጠላ አልተወለደም፡፡›› ተስፋየም እርግጠኛ ነኛ አማራን ሊጠላ አልተወለደም ካባንዳ አያቶቹ ተማረዉ እንጅ፤፤

No comments:

Post a Comment