Thursday, August 13, 2015

1. ጀኔራል ሳሞራ የኑስ

        ያኔው ብላቴና ሳሞራ የኑስ በድንቁርናው ምክኒያት እስከ መጨርሻው ከትምህርቱ ከተሰናበተ በኋላ የወላጆቹም የእሱም ተስፋ መክኖ ዘንባባና አከት ከመሸጥ በስተቀር ምንም አይነት የሕይወት አማራጭ በማጣቱ በነሀሴ ወር 1968 ዓ.ም ወደ ደደቢት በረሃ በመውረድ ህወሓትን ተቀላቀለ፡፡
በደካማ ጎኑ ዝና ለማፈስ የታደለው ሳሞራ የኑስ ህወሓትን በተቀላቀለ በአጭር ጊዜ ውስጥ በፈሪነቱ ሀገር ያወቀው ፀሀይ የሞቀው ሆነ፡፡ እንደ መለስ ዜናዊ እሱም በተደጋጋሚ ከጦር ሜዳ ሸሽቷል፡፡ የጥይት ድምፅ ሲሰማ የያዝውን መስሪያ አፍሙዝ አዙሮ የአፅፋ መልስ ከመስጠት ይልቅ ጠብመንጃውን ወርውሮ መሸሽጊያ ጥግ ፍለጋ እንደሚጣደፍና በፍርሃት እንደሚርበተበት በቅርብ የሚያውቁት የትግል ጓዶቹ ይናገራሉ፡፡
በድድብናው ከትምህርት ቤት የተባረረው ሳሞራ የኑስ በህወሓት ውስጥ በፍሪነቱ በጦር ሚዳ ባሳየው ነውረኛ ባህሪ ምንም አይነት እርምጃ አልተወሰደበትም፡፡ ይልቁንም የእሱ ቢጤ ፈሪ ለሆነው መለስ ዜናዊና ስብሃት ነጋ ጭምር ጆሮ ጠቢ ሆኖ በታማኝነት በማገልገሉ ባንድ ጊዜ ሀይል መሪ ለመሆን በቅቷል፡፡ ቀጥሎም ፀረ-መለስ ዜናዊ እንቅስቃሴ ያደርጋሉ ብሎ በመፈረጅ በርካታ ታጋዮችን በማስረሽኑ የክፍለ ጦር አዛዠ ሆኖ ተሸሟል፡፡
ሆኖም ሳሞራ የኑስ የወታደራዊ አዛዠነቱን ቦታ ይያዝ እንጂ አንድም ጊዜ እራሱን ችሎ ያዋጋበት ጊዜ የለም፡፡ በሚመራው ስራዊት እጅግ በጣም የሚጠላ፣ ሁሉም የሚያዋርደው እና መሳቂያ መሳለቂያ የሚያደርገው ነበር፡፡
ሳሞራ የኑስ በቅርቡ በ1991 ዓ.ም ከኤርትራ ጋር በተደረገው ጦርነት ገና አንድ ጥይት ሲተኮስ ከዛላንበሳ ግንባር ፍርጥጦ አዲግራት በመግባቱ የሚመራውን ክፍለ ጦር ሙሉ በሙሉ አስደምስሶታል፡፡
ሳሞራ የኑስ አሁንም ቢሆን እስከ ጀነራልነት ማዕረግ ደርሶ የመከላከያ ኤታማጆር ሹም ለመሆን የበቃው ለመለስ ዜናዊ ባለው ታማኝነት ብቻና ብቻ ነው፡፡በመሆኑም መለስና ተከታዪቹ በእነሱ ግምት ለወደፊቱ የስልጣን ህልውናቸው ስጋት የሚደቅኑ አባላትን በማስረሸን ያስወገዷቸው በሳሞራ የኑስ አማካኝነት ነው፡፡ ሀየሎም አርአያን ጨምሮ፡፡
ሱዳናዊው ሳሞራ፤ ኤርትራ ሳህል ከርከበት የተወለደው ሳሞራ፤ ዘንባባና አከት ከጫካ እየለቀሙ የሚሸጡ እጅግ በጣም ችግረኛ ወላጆች ስለነበሩት አንድ ቀን ጠግቦ በልቶ የማያውቀው ሳሞራ፤ የአብረሃ ወአፀብሃ ዝነኛው ደድብ ተማሪና በህወሓት ውስጥ በፈሪነቱ ስሙ ገናና የሆነው ሳሞራ፤ የዛሬው የጦር ሳይንስ መሀይም የመጀመሪያው ጀነራል ሳሞራ የኑስ ከእግር ጥፍሩ እስከ ጭንቅላት ፀጉሩ ድረስ በወንጀል የጠለቀ ነው፡፡ ቂመኛ በመሆኑ ፈሪነቱን ሊያጋልጡ የሚሞክሩ በርካታ ታጋዮችን ጊዜ እየጠበቀ ሰበብ አስባብ በመፍጠር ረሽኗቸዋል፡፡
ሳሞራ የኑስ ሰነፍ፣ ፈሪና አድርባይ ብቻ ሳይሆን ሴሰኛም እንደሆነ ይነገራል፡፡ በበረሃ በርካታ የህወሓት ታጋይ የሆኑ ሴቶችን ድፍሯል፡፡ ይባስ ብሎ የተደፍሩት ሴቶች እንዳያጋልጡት ቀድሞ የፈጠራ ክስ በመመስረት ሐለዋ ወያኔ ወደተሰኝው አደገኛ እስር ቤት ይልካቸውና በዚያው ይረሸናሉ፡፡ ለአብነት ያክል በ1974 ዓ.ም ርግበ ሰለሞን እና ፀጌ ሰለሞን የተባሉትን ታላቅ እና ታናሽ እህትማማቾች በየተራ ካባለገ በኋላ ነውረኛ ተግባሩ ሊጋለጥበት ሲሆን “ሁለቱ ሴቶች አደገኛ ህንፍሽፍሾች ናቸው” በማለት ወደ ፃኢ ሀለዋ ወያኔ ልኳቸዋል፡፡ ከዚያም ጉዳዩ ወደስብሃት ነጋ ተላልፎ ስብሃት ነጋ ሁለቱን እህትማማች ሴቶች አንድ ጉድጓድ ውስጥ ገብተው ተጋድመው በጥይት ተደብድበው እንዲገደሉ አድርጓል፡፡
ሳሞራ የኑስ ዛሬም የመኪናውን የሰሌዳ ቁጥር በጥቁር ፕላስተር እየለጠፈ በየሴተኛ አዳሪዎች ቤት እንደሚልከሰከስ ብዙዎቹ ይመሰክራሉ፡፡

No comments:

Post a Comment