Saturday, August 29, 2015

የተደበቀው የህወሓት ማንነት ከደደቢት እስከ ቤተ መንግስት (ክፍል 4) – የሜ/ጀነራል ሞላ ኃ/ማርያም; የጌታቸው አሰፋና ኢሳያስ ወ/ጊዮርጊስ ገመና - See more at: http://www.zehabesha.com/amharic/archives/46239#sthash.rQL6FCDf.dpuf

Molaሜጀር ጀነራል ሞላ ኃ/ማርያም ሞላ ኃ/ማርያም በትጥቅ ትግሉ ወቅት ልክ እንደ አበበ ተ/ኃይማኖት ሓለዋ ወያኔ ወይም ባዶ ስድስት እየተባለ በሚጠራው አደገኛ የማሰቃያ እስር ቤት ውስጥ ተመድቦ ይሰራ ነበር፡፡ ጠውቆ ከሚባል ቦታ የተቋቋመውን አደገኛ እስር ቤት እዲጠብቁ ተመርጠው ከተመደቡት 500 ታማኝ የህወሓት ታጋዮች የ250ዎቹ አዛዥ ሞላ ኃ/ማሪያም ነበር፡፡ በመሆኑም በየጊዜው ወደ አደገኛው ወህኒ የሚገቡ እልፍ አዕላፍ ታጋዮችን እሱ በሚያዘው በጥበቃ ስም በተደራጀ ገዳይ ቡድን በጥይት እያስጨፈጨፈ ለዓመታት ኖሯል፡፡ ሞላ ከሚያዘው ገዳይ ቡድን እስረኞቹን በግፍ ከማስረሸኑ ባለፈ ራሱም በሽህ የሚቆጠሩ “የአማራ ብሄር” ተወላጆችን በአንድ ላይ ሰብስቦ በማቆም መትረየስ ጠምዶ በእሩምታ ተኩስ ጨፍጭፎ በጅምላ እዲቀበሩ አድርጓል፡፡ ሞላ ኃ/ማሪያም በህወሓቶች የሽፍትነት ዘመን በእስር ቤት ሰዎችን ከመረሸንና የገዳይ ቡድኑ መሪ ከመሆን እና ስብሃት ነጋና መለስ ዜናዊን በአጃቢነት ከማገልገል የዘለለ ሚና አልነበረውም፡፡ ምንም አይነት ጦርነት ላይ አልተካፈለም ነበር፡፡
ነገር ግን በርሃ ወርዶ የባንዳውን ቡድን ህወሓትን ሲቀላቀል የትምህርት ደረጃው ከ8ኛ ክፍል በታች የነበረው ሞላ ኃ/ማሪያም የጀነራልነት ማዕረግ አግኝቶ የአየር ኃይል አዛዥ ሆነ፡፡ ከህወሓት የጦር መሀይማን ጀነራሎች አንዱ የሆነው ሞላ ከኮሎኔልነት ማዕረግ ወደ ጀነራልነት ሊያድግ የቻለው የሁለት ልጆቹን እናት ለአበበ ተ/ኃይማኖት በቅምጥነት ስጦታ በመስጠት ነው፡፡ እሱም ልክ እንደ ሳሞራ የኑስ፣ አበበ ተ/ኃይማኖትና ሌሎች የህወሓት ባለስልጣናት የወጣለት ሴሰኛ ነው፡፡ በአየር ኃይል ጠ/መምሪያ ውስጥ የሚሰሩ ባለትዳር ሴቶችን አባልጓል፡፡ ባለቤቱም ከቤት ሰራተኛው ጋር ተኝቶ መኝታ ቤታቸው ውስጥ እጅ ከፍንጅ ይዛዋለች፡፡ ሞላ ኃ/ማሪያም የአየር ኃይል አዛዥ በነበረበት ወቅት በርካታ የዘረፋ ወንጀሎችን ፈፅሟል፡፡ በአንድ ወቅት የአሜሪካ መንግስት ለአየር ኃይሉ አብራሪዎች በጠቅላላ ስልጠና ሊሰጥ ስምምነት ላይ ይደርስና የአሜሪካ አየር ኃይል አባላት የሆኑ ከፍተኛ ሙያተኞች ወደ ኢትዮጵያ ይመጣሉ፡፡ ከዚያም አሜሪካውያኑ ለበረራ ልምምድ የሚውል ብዛት ያለው ነዳጅ እዲገዙና በደረሰኙ መሰረት እደሚያወራርዱላቸው ሞላንና ሌሎችን የአየር ኃይሉ አመራሮች የሆኑ የህወሓት ሰዎችን ይነግሯቸዋል፡፡ የአየር ኃይሉ ዋና አዛዥ የሆነው ሞላ አሜሪካዊያኑን እደምንም አሳምኖ ገንዘቡን ቅድሚያ እዲሰጡዋቸው በማድረግ ለስልጠናው የሚያስፈልገውን ነዳጅ ከዚያው ከአየር ኃይል ዴፖ በመሙላት ከፍተኛ ቁጥር ያለውን ዶላር ለግሉ አድርጎታል፡፡ ሞላ ኃ/ማሪያም በ2005 ዓ.ም ለሆራ አየር ኃይል ሆስፒታል በሚሊዮኖች ዶላር ከውጭ ተገዝተው የገቡ ሙሉ የህክምና ቁሳቁሶችን ከመጋዘን አውጥቶ ሸጧል፡፡ የህክምና ቁሳቁሶቹን በሌሊት ከሆስፒታሉ መጋዘን ወጥተው በመኪና ተጭነው ሲጋዙ ተረኛ ሀኪም ሆኖ በአጋጣሚ የተመለከተውን የጉራጌ ተወላጅ የሆነውን አምሳ አለቃ ሰለሞንን ሞላ ሻለቃ ገ/ህይወት /ወዲ ራያ/ የተባለውን የአየር ኃይሉን የደህንነት ኃላፊ ልኮ አስገድሎታል፡፡ በህወሓት የሽፍትነት ዘመን የወጣለት ገዳይ፣ የአፋኝና ረሻኝ ቡድን መሪ የነበረው ሞላ ኃ/ማሪያም የአየር ኃይል አዛዥ በነበረበት ወቅት በርካታ የአየር ኃይል አባላትን በስውር እዲገደሉ አድርጓል፡፡ ለምሳሌ፡- በ2001 ዓ.ም ለግል ቪላ ቤት መገንቢያ ታስቦ ሲሚንቶ፣ ብረትና ቆርቆሮ ከአየር ኃይል ግቢ በሌሊት ተጭኖ ሲወጣ የተመለከተው ሻምበል ዓለሙ የተባለ የጥበቃ ሰራተኛ ሆን ተብሎ በመኪና ተገጭቶ እንዲገደል አድርጓል፡፡ ከሽሬ ሰለክላካ አርሶ አደርነት የአየር ኃይል አዛዥ የሆነው ሞላ ኃ/ማሪያም ሓለዋ ወያኔ /ባዶ ስድስት/ አደገኛ እስር ቤት ውስጥ በቆየባቸው ረጅም ዓመታት ውስጥ ግድያና ዘረፋን በሚገባ ተክኖታል፡፡ በአየር ኃይል ጠ/መምሪያ ግቢ መጋዘን ውስጥ ተከማችቶ የነበረ በርካታ የጦር መሳሪያ ክላሽን ኮቭና ሽጉጥ ከነመሰል ጥይቶቹ በድብቅ አውጥቶ ለሆራ አርሰዲ፣ ጨፌ፣ ዝቋላና አካባቢው ገበሬዎች ቸብችቦታል፡፡ ከባህር ማዶ ነዳጅ የመጣባቸውን በርሜሎች አሰብስቦ በጨረታ እዲሸጡ በማድረግ ገንዘቡን ከተባባሪዎች የህወሓት ሰዎች ጋር ተከፋፍሎታል፡፡ ሙልጭ ያለው ሌባ ጀነራል ሞላ ኃ/ማሪያም ከአፄ ኃይለስላሴ ጀምሮ በአየር ኃይል ግቢ ውስጥ የነበሩትን ባለ ግርማ ሞገስ ግዙፍ፣ ግዙፍ ዛፎችንም አስቆርጦ ሸጦ በልቷቸዋል፡፡ ማፍያው ጀነራል ሞላ ኃ/ማሪያም በተለያዩ ጊዜያት በተደጋጋሚ የአየር ኃይሉን ንብረቶች በሌሊት አስጭኖ በማስወጣት እየሸጠ በሌቦች ተዘረፈ አስብሏል፡፡ ለአብነት በ2002 ዓ.ም በተደጋጋሚ የተደረጉትን የኮምፒውተሮችና ሌሎች በከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ከውጭ የሚገቡ ቁሳቁሶችን ዘረፋ ማስታወሱ ብቻ በቂ ምስክር ነው፡፡ በየጊዜው ከቻርተር በረራዎች /ከኪራይ/ የሚገኘውን ወፈር ያለ ገቢ ሞላ ኃ/ማርያም ወደግል የባንክ ሂሳቡ እንዲጨመር አድርጓል፡፡ ለምሳሌ ባንድ ወቅት “የናሽናል ጂኦግራፊ” አዘጋጆች ወደ ኢትዮጵያ መጥተው ሄሊኮፕተር በመከራየት ወደ ኤርታሌ አምርተው ነበር፡፡ ታድያ የህዝብ ንብረት ከሆነው ሄሊኮፕተር ኪራይ የተገኘውን ገቢ ሞላ ኃ/ማርያምና ሌሎች የአየር ኃይሉ ቁንጮ የሆኑት ህወሓቶች በመዝረፍ ጮማ ቆርጠውበታል ዊስኪ ተራጭተውበታል፡፡ ሞላ እና በአየር ኃይሉ ውስጥ የሚገኙ የህወሓት መኮንኖች ከራሱ ከአየር ኃይል በዘረፉት ገንዘብ የገዟቸውን መኪኖች ለአየር ኃይሉ አከራይተው ከፍተኛ ገንዘብ አጋብሰዋል፡፡ አየር ኃይሉ ለሠራተኞቹ የትራንስፖርት አግልግሎት የሚሰጡ የራሱ መኪኖች እንዳይኖሩት የተደረገው ሆን ተብሎ ለዚህ ዓላማ ነው፡፡ ሞላ ኃ/ማሪያምና ሌሎች ህወሓታዊያን የአየር ኃይሉ ሹማምንቶች ቅልብ አብራሪዎች በመባል ይታወቃሉ፡፡ ሜጀር ጀነራል ሞላ ኃይለ ማርያምንና መሐሪ ዘውዴን እጃቸውን ይዞ የበረራ ትምህርት ያስተማራቸው የቀድሞው ሰራዊት አባል መቶ አለቃ እንደገና ታደሰ ነው፡፡ ጀነራል ሞላ ኮሎኔል በነበረበት ወቅት በቀድሞው አየር ኃይል አባልና የምክትል መቶ አለቅነት ማዕረግ ባለው ዮናስ በላይ /ደቦራው/ ይመራ ነበር፡፡ ጌታቸው አሰፋ ጌታቸው አሰፋም እንዲሁ አበበ ተ/ኃይማኖትና ሞላ ኃ/ማሪያም በህወሓት የሽፍትነት ዘመን ሐለዋ ወያኔ የተባለው ጋሃነም አለቃ ነበር፡፡ ጌታቸው አሰፋ በሓለዋ ወያኔ /ባዶ ስድስት/ አደገኛ ወህኒ ውስጥ በርካታ ኢትዮጵዊያን ላይ አያሌ ሰቆቃዎችን ፈፅሟል፡፡ ተለይተው እየታፈሱ ወደ አደገኛው ወህኒ በየጊዜው የሚገቡ “የአማራ ብሄር” ተወላጆችን አንድ ላይ ሰብስቦ ላያቸው ላይ መትረየስ በማርከፍከፍ ጨፍጭፏቸዋል፡፡ የገሀነሙ አለቃ ጌታቸው አሰፋ ሓለዋ ወያነ ባዶ ስድስት አደገኛ ወህኒ ውስጥ ቁጥር ስፍር የሌላቸውን ታሳሪዎች በፋስ ጭንቅላታቸውን ተርትሯል፣ ሙሉ አካላቸውን በፈላ ውሃ አንፍሯል፣ ብልታቸውን በጋለ ብረት አቃጥሏል፡፡ ጌታቸው አሰፋ ዛሬም በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ ሰቆቃ፣ አፈና እና ግድያ እየፈፀመ የሚገኘው የህወሓት ደህንነት ቢሮ ዋና ተጠሪ ነው፡፡ ኢሳያስ ወ/ጊዮርጊስ እንደ አብዛኞቹ የህወሓት ባለስልጣናት ትምህርቱን ከ9ኛ ክፍል ያቆመው ኢሳያስ ወ/ጊዮርጊስ እሱም እጆቹ በንፁህ ኢትዮጵያዊያን ደም የተጨማለቁ ወንጀለኛና የለየለት ነብሰ በላ ነው፡፡ በህወሓት የሽፍትነት ዘመን በ1980 ዓ.ም ከትግራይ ውጭ ላለው የኢትዮጵያ መሬት አንዋጋም ካሉት ታጋዮች ውስጥ 36 ሺህዎቹ ሲረሸኑ ኢሳያስ ወ/ጊዮርጊስ ከገዳዮቹ አንዱ እደሆነ ምስጢሩን የሚያውቁ የትግል ጓዶቹ ይመሰክራሉ፡፡ ኢሳያስ ወ/ጊዮርጊስ በአሁኑ ጊዜም ከጌታቸው አሰፋ ቀጥሎ የህወሓት ደህንነት ቢሮ ሁለተኛ ሰው ሲሆን በደህንነቱ ውስጥ በስውር ተደራጅቶ የአፈና፣ ግድያና ድብደባ ተግባር የሚፈፅመው ቡድን የሚታዘዘው በእሱ ነው፡፡ ኢሳያስ ወ/ጊዮርጊስ የ1997 ዓ.ም ምርጫ ውጤትን መጭበርበር ተከትሎ በተነሳው ህዝባዊ ተቃውሞ እሱ የሚያዘውን ገዳይ ቡድን ከአግአዚ ኮማንዶ ጋር አቀናጅቶ በመምራት ህፃናትና ወጣቶችን በጥይት እስጨፍጭፏል፡፡ ህወሓት እንደ ጌታቸው አሰፋና ኢሳያስ ወ/ጊዮርጊስ አይነት ከበርሃ ጀምሮ በአረመኔነታቸው የሚታወቁ ተኩላዎችን አሰማርቶ ነው የኢትዮጵያን ህዝብ በሰቆቃ፣ አፈና፣ ግርፋትና ግድያ ረግጦ እየገዛ ለ24 ዓመታት የዘለቀው፡፡ - See more at: http://www.zehabesha.com/amharic/archives/46239#sthash.rQL6FCDf.dpuf

No comments:

Post a Comment