• ሁሉም የኮሜቴው አባላት ለነሐሴ 4 ቀን 2008 ዓ.ም. ቀጠሮ ተሰጧቸዋል
• ፖሊስ አስለቃሽ ጪስ እየተጠቀመ ነው
ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ ፍርድ ቤት ቀርበዋል በሚል በብዙ ሽዎች የሚቆጠሩ ዐማሮች በሰሜን ጎንደር ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዛሬ ረፋዱ ላይ ተሰባሰቡ፡፡ ፍርድ ቤት ጉዳዩን ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ በሌሉበት ሊመለከተው መሆኑን ያወቁት የጎንደር ሕዝብ ፍርድ ቤቱ ሳይዘጋ ኮሎኔል ከሳሽ ካለውም ይከሰስ ከሌለውም በቶሎ ወደ ቤተሰቦቹ ይመለስ የሚል ጥያቄ በፍርድ ቤቱ አቅራቢያ ጩኸት በረከተ፡፡ 
የአድማ ብተና ፖሊስ የፍርድ ሒደቱትን ለመከታተል በመጣው የዐማራ ሕዝብ ላይ የኃይል ርምጃ መውሰድ ሲጀምር የወጣቶቹ ቁጣ ገነፈለ፡፡ የፍርድ ቤቱ መስኮቶች በድንጋይ ረጋገፉ፡፡ ወያኔ ሌቫ፤ ወልቃይት ዐማራ… ወዘተ የሚሉ የዐማራ ተጋድሎ ድምጾች በመለዋ የጎንደር ከተማ ከጫፍ ጫፍ ተስተጋባ፡፡ ጎንደር የሚገኘውን የወያኔ ደኅንነት ቢሮ አካባቢ የተጋድሎ ሠልፍ በረከተ፡፡ ፒያሳና መስቀል አደባባይ በአንድ ሳምንት ብቻ ሁለት ጊዜ ዐማሮች ጩኸታቸውን ማሰሚያ መድረክ ሆኑ፡፡ 
እስከዚህ ሰዓት ድረስ በሰው ሕይወት ላይ የደረሰ አደጋ ባይኖርም የአድማ ብተና ፖሊስ አስለቃሽ ጭስ ከመጠን በላይ በዐማሮች ላይ እየበተነ ነው፡፡ ከተጋድሎው ተሳታፊዎች መካከል አንድ ሰው ከፍተኛ አደጋ የደረሰ ቢሆንም አሁን ላይ በሙሉ ጤንነት መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡ 
ይህ በዚህ እንዳለ ፍርድ ቤቱ ለነሐሴ 4 ቀን 2008 ዓ.ም. ኮሎኔል ደመቀ በሌሉበት ጉዳያቸውን እንዲታይ ወስኗል፡፡ ኮሎኔል ደመቀ ከማረሚያ ቤት ሆነው በቪዲዮ ኮንፈረንስ (ፕላስማ) ለፍርድ ቤቱ ከሳሽ ከቀረበባቸው ይከላከላሉ፤ ካልቀረበም ፍርድ ቤቱ ወሳኔ ይሰጣል የሚል መልስ ቢኖርም የጎንደር ከተማ ሕዝብ አሁንም ተቃውሞውን እያሰማ ነው፡፡ 
በተያያዘም በማእከላዊ ፍርድ ቤት ያሉት የታፈኑ የወልቃይት ጠገዴ ዐማራ ማንነት ኮሚቴ አስተባባሪዎችም ነሐሴ 4 ቀን 2008 ዓ.ም ፍርድ ቤት ይቀርባሉ፡፡ አዲስ አበባ ማእከላዊ ታፍነው የሚገኙት የኮሜቴው አባለት አቶ አታላይ ዛፌ፣ አቶ ጌታቸው አደመ፣ መብራቱ ጌታሁን፣ አቶ አለነ ሻማ፣ አቶ አዲስ ሰረበ እና አቶ ነጋ ባንቲሁን ናቸው፡፡ 
አዳዲስ ነገሮችን በየሰዓቱ እናቀርባለን፡፡ 

No comments:
Post a Comment