Monday, June 27, 2016

ሰበር መረጃ.. በመፍረስ እና በመሸሽ ላይ የሚገኘዉ ህወሃት !



እራሱን የትግራይ ነጻ አዉጪ ቡድን እያለ የሚጠራዉ የወያኔ ስርአት ዋነኛ የጀርባ አጥነት የብሔራዊ መረጃ በዘረፋና በሽሽት ተጠምዷል። 
በሰሞኑ የህዉ የብሔራዊ መረጃ 9 ሚሊዮን ዶላር ወጪ በማድረግ በአለም ዙሪያ የሚገኙ የህወሃት የመረጃ ክንፍ ቀድሞ የሰየማቸዉንና በስለላ ስራ ላይ ተሰማርተዉ የነበሩ የሌላ ብሔር አባላቶችን በሙሉ መልሶ ወደ ሐገር ቤት በማስገባት በምትካቸዉ ከ 242 የሚጠጉ የአንድ ብሔር ብቻ ተወላጅ የሆኑ የመረጃ ሰራተኞችን እየተካ ይገኛል።
ጉዳዩን በትኩረት የተመለከቱት መረጃዎቻችን የመፍረስ ወይም የሽሽት መንፈስ እንዳለዉ የሚናገሩለት ይህ ዝዉዉር ድንገተኛና ያልተገመተ እንዲሁም ከፍተኛ የሆነ የገንዘብ ወጪ እየተደረገበት መሆኑ እጅግ እንዳሳሰባቸዉ ጠቅሰዉ እነዚህ ወደ ተለያየ ሐገር የሚላኩት የአንድ ብሔር የስለላ አባላቶች በትምህርት ፍቃድ ( Study Permit ) በንግድ ፍቃድ ( Business Permit ) በበቤተሰብ ጉብኝት ወይም ትስስር ፍቃድ ( Relation Permit ) በስራ ፍቃድ ( Work Permit ) በመንግስታዊ የስራ ወይም በዲፕሎማቲክ አገልግሎት ፍቃድ ( Diplomatic Travel documents ) ሲሆን በዋነኛነት የአሜሪካን ዋሺንግተን ዲሲ የአዉሮፓዎቹ ኖርዌይና ብሪታኒያ እንዲሁም የመሳሰሉት እና ደቡብ አፍሪካ አዉስትራሊያ የዝዉዉሩ ትኩረቶችእንደሆኑ ለማወቅ ተችሏል።
የብሔራዊ መረጃ ከፍተኛ አመራሮች የህወሃት ባለስልጣን ቤተሰቦችና የትዳር ጓዶች ባጠቃላይ የተካተቱበት ይህ ሽሽት ወይም ዘረፋ ከዚህ ቀደም በሐገሪቷ ላይ ከታዩ አይን ያወጡ የዘረኝነት መንፈሶች ለየት ያለ እና እጅግ የተቻኮለ ሲሆን በተለያየ አለም ከሚገኙ የመረጃ ሰራተኞች ዉስጥ እስከ 23/06/2016 ወደ ሐገር ቤት እንዲመለሱ ከተጠሩት ዉስጥ በአብዛኛዉ እየተሰወሩ መሆኑና የመመለሻ ጊዜያቸዉም ማለፉን ታማኝ ምንጮቻችን አረጋግጠዋል።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ ! !
( ጉድሽ ወያኔ )

No comments:

Post a Comment