Saturday, February 13, 2016

እውን ጥላሁን ገሠሠን በስለት ለመወጋት ያበቃው የ’ሆድ ይፍጀው’ ምስጢር ይህ ይሆን ልዑል ዓለሜ የተባሉ የዘ-ሐበሻ ተከታታይ ጥላሁን ገሰሰ እስከ እለተ ሞቱ ድረስ አፍኖት የሞተው ምስጢር ‘ሆድ ይፍጀው” ጉዳይ ይህ ነው በሚል አንድ ጽሁፍ አድርሰውናል:: ጥላሁን በሕይወት ስለሌለ አሁንም ይህንን ጉዳይ ከርሱ አንደበት ማረጋገጥ ባይቻልም የጸሀፊውን ምስጢራዊ ጽሁፍ ለግንዛቤ አስተናግደናል::የጥላሁን ገሰሰ ( ሆድ ይፍጀዉ ) ሚስጥር የወጋ ቢረሳ የተወጋ አይረሳ ! !


ጥላሁን ገሰስ መስከረም 27 1940 ዓ/ም ከእናቱ ከወ/ሮ ጌጤ ጉርሙ ከአባቱ ከአቶ ገሰሰ ወ/ኪዳን ተወልዶ በሚያዚያ 9/2009 ዓ/ም ከዚህ አለም በክብር ተሰናብቷል የመጀመሪያ የሙዚቃ ስራዉን በሐገር ፍቅር ቲያትር የቀረበዉ፡ የኢትዮጵያ የሙዚቃ ንጉስ ክቡሩ ሰዉ አርቲስት ጥላሁን ገሰሰ በ1960ዎቹ አመተ ምህረት አካባቢ ነበር እጅግ ታዋቃና ወርቃማናቱን በወርቃማዉ እድሜዉ ዘመን ላይ ጊዜ የማይሽረዉን አሻራ ያስቀመጠዉና ያሳየዉ ጥላሁን በዚያን በ60ዎቹ ዘመን ላይ በቅጽል ስም ዘ ቮይስ “The Voice” ተብሎ ይጠራ ነበር።
በ1970 እና 80 አካባቢዎች ላይ በሐገር አቀፍ ደረጃ ወሳኝ እና ቀስቃሽ ሙዚቃዎችን ለወገኖቹ አብርክቷል አርቲስት ጥላሁን ገሰሰ በዚሁ ሐገር ወዳድነቱና ፍቅሩ የተንሳ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የዶክተሬት ማእረግ ከማግኘቱም ባሻገር የስነ ጥበብ ማእከላ ( Ethiopian Fine Art and Mass Media Prize Trust. ) የክብር ሽልማት ባለቤት ነዉ።

ጥላሁን ገሰሰ ስላዘፈነዉ ነገር የለም ከቀጠሮ ጀምሮ እስከ እስከ ስራ ክቡርነት የተዳሰሰዉ በጥላሁን ገሰሰ ዜማና ድምጽ ነበር፡ ጥልዬ በደርግ ዘመነ መንግስት በሐገሪቱ ዙሪያ በተቀሰቀሰ ጦርነት ምክንያት እጅግ ቀስቃሽ ወታደራዊ ሙዚቃዎችን ግንባር ድረስ ሄዶ በማቅረብ የሚታወቅ ታላቅ የአርት አባት ነበር።
ሚያዚያ 18/1993 የኢትዮጵያዊያን ፋሲካ እለት እሁድ ማምሻዉን በአስገራሚ ሁኔታ አርቲስት ጥላሁን ገሰሰ በመኖሪያ ቤቱ ዉስጥ በስለት ተወጋና ተገኘ።
የዚያን እለት ከቀኑ 4 ሰአት ላይ እስጢፋኖስ ቤ/ክርስቲያን ፊት ለፊት አይሴማ ሕንጻ ስር በምትገኘ ሰለሞን ካፌ ዉስጥ አሉ የሚባሉ አንጋፋዎች ተሰባስበዋል ሰለሞን የካፌዋ ባለቤት ሚስቱ በኮሞሮስ ደሴት ላይ ከተከሰከሰዉ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አደጋ የዳነች በወቅቱ ብቸኛ ሐብታምና የሙሶ መኪና አስመጪ፣ ሐየሎም አርአያ፣ መሐመድ አል_አሙዲን፣ እንዲሁም እዚያዉ አይሴማ ህንጻ ላይ ይኖር የነበረዉ ታደለ ይድነቃቸዉ፣ ጥላሁን ገሰሰ፣ እና የጃክሮስ ባለቤት በአንድነት ሆነዉ ሻይ እየጠጡ ተቀምጠዉ ነበር። መሐመድ አል_ አሙዲን በወቅቱ እዚያ ያዘወትር የነበረበት ምክንያት ሜላት የተባለች እጮኛዉ ( ሜላት ኮምፒዉተር ) እዚያ ሕንጻ ላይ 5ተኛ ፎቅ ተከራይታ ትኖር ስለነበር ሲሆንና የሻራተን ሆቴል በቁፋሮ ላይ ስለበር በቅርበት ለመቆጣጠርም ጭምር ነዉ።

የሻይ ቡና ፕሮግራሙ ሞቅ ደመቅ እያለ በነበረበት ወቅት አንድ የስልክ ጥሪ ከወደ ካፌዉ ወደ ጥላሁን አቃጨለች ጥላሁን የስልኩን ጥሪ ካስተናገደ ወዲህ ፊቱ ልዉጥውጥ ብሎ የነበረበት ቦታ ተቀመጠ ጉዳዩን በአንክሮ የተከታተለዉ ሀየሎም ጥላሁንን ለብቻዉ ገለል አድርጎት ምን እንደተፈጠረ ይጠይቀዋል ጥላሁንም ሌሎቹ በጥቂቱ እንደሚሰሙት እያወቀ፣…
” አነተ ዉሻ የዉሻ ልጅ!!! ተነስ ታጠቅ ዝመት እያልክ የትግራይን ህዝብ ደም ስታፈስ ኖረህ አሁን ምንም እንዳልተፈጠረና እንዳልሰራህ እዚህ ሐገር ላይ በሰላም ትኖራለህ ? በፍጹም አትኖርም “….. ሲል አንድ ግለሰብ አስፈራራኝ በማለት ይናገራል!
ሐየሎም ጥላሁን አተኩሮ ከተመለከተዉ በኋላ ደንገጥ እንደማለት ብሎ ዝምታን በመምረጡ ጥላሁን ቀደም ብሎ ሁሉንም ተሰናብቷቸዉ ሄደ! ሐየሎምም እሳት ጎርሶ እሳት ልሶ ” እነዚህ የዉሻ ልጆች አርፈዉ አይቀመጡም ” በማለት ተሳድቦ ከጥላሁን ገሰሰ እግር ተከትሎ ሄደ።

እንግዲያዉ ማታ ጥላሁን ገሰሰ በብሔራዊ ቲያትር ዉስጥ እይዋት ስትናፍቀኝን በማንቆርቆር ህዝብን ሲያስደስት በነበረበት ወቅት ላይ የተደገሰዉ የግድያ ሴራ በሐየሎም አረያ ጣልቃ ገብነት ተሰናከለ! ነገር ግን ግድያዉን ሳይፈጽሙ ላይተኙ ቃል የተገባቡት የጠቅላይ ሚኒስቴሩ ሳጥናኤሎች ወደ መኖሪያዉ ቤት በማምራት ተንኮላቸዉን ፈጸሙ በዚያዉ የሞት ድግስ ላይ አትለፊ ያላት የጥላሁን ገሰሰ ህይወት ግን እለቱን ተሻገረች ጥላሁን ለህክምና ከሐገር ሲወጣ በቁፋሮ የተገኘዉ የሐገራችን አንጡራ ሐብት ጥላሁንን አጅቦት ኮበለል።
ሞት ለወያኔ!

No comments:

Post a Comment