Thursday, February 25, 2016

የአባይ ወልዱ በወልቃይት ጠገዴ ሕዝብ ላይ የጦርነት ነጋሪት መጎሰም የህይወት ዋጋ ያስከፍላል! | ጎንደር ህብረት


ጎንደር ህብረት
የትግራይ ነጻ አዉጭ ግንባር ብሎ እራሱን የሚጠራዉ ድርጅት መሪ አቶ አባ ወልዱ እና የክልሉ የፀጥታና የአስተዳደር ኃላፊ አቶ ሐድስ ዘነበ ከዘራፊ ካድሬወቻቸው ጋር በመሰባሰብ፤ በወልቃይት፤ በጠገዴ እና በጠለምት ህዝብ ላይ የማያዳግም ጦርነት ለማካሄድ የጦር ነጋሪት እየደለቁ በማስፈራራት ላይ ይገኛሉ። ጦርነቱን በሚፈልጉት መንገድ በድል ለመወጣት እየተጠቀሙበት ያለው የሞራል መምቻ ደግሞ፤ ህብረተሰቡን፤ በገብያ፤ በቤተክርስቲያን እና ቤት ለቤት በማደን እያስፈራሩ ወደፖሊስ ጣቢ እየወሰዱ፤ ወልቃይት የትግራይ ክልል እንደሆነች እንድትቀጥል እንደሚፈልጉ በማሥመሰል በማሥገደድ እያስፈረሙ ናቸው።
Gondor Hibret
ሌላ የዚህ ሳምንት አስገራሚዉ የወያኔ ቲያትር ደግሞ፤ ከስህተት ላይ ሥተት በመደራረብ ህዝብና ህዝብን ለማጋጨት የትግራይ ተወላጆችን ስልፍ አሰልፎ በጉልበት ይዞት የቆየዉን መሬት የትግራ ነዉ እያለ ማስጨፈሩ ነዉ። ወያኔ በመላዉ ኢትዮጵያ ሰልፍ ከልክሎ ሰላማዊ ሰልፈኞችን በታንክና መትረየስ እዬጨፈጨፈ፤ ጎንድር መሪ የሌለዉ መሆኑን የተረዳዉ ወያኔ ወገራ አዉራጃ ላይ የትግራይ ተወላጆችን ከጎንደር ህዝብ ጋር ቂም ለመትከል የዉሸት ሰልፉን አቀነባብሮ ያስጨፍራል። የተቃዉሞ ስሜትን በአደባባይ መግለጽ ከሆነማ ይህ አይነቱ ወልቃይት ጠገዴ እና ጠለምት ብሎም ለመላዉ ጎንደር/ አማራ ህዝብ መፈቀድ የግድ ይላል።
ጦረኛ ቡድን በአሁኑ ሰዓት ሌላ ወንጀል እና ደባ ከመፈጸም ይልቅ፤ መደረግ የነበረበት፤ የወልቃይት፤ የጠገዴ እና የጠለምትን ህዝብ ባለፉት 25 ዓመታት በተፈጸመበት ግፍና በደል ይቅርታ መጠየቅ ነበር እንጂ አድሮ ጥጃ የሆነዉ የትግራይ ነፃ አዉጭ ግንባር የአማራን መሬት በሰፊዉ ለመቆጣጠር የጦርነት ክተት አዋጅ ነጋሪት መደለቅ እና በቴለቭዥን መስኮት ውሸት መርጨት አልነበረበትም። ይህ ድርጊት ታሪክ ይቅር የማይለው አሳዛኝ ተግባር ነው። ለዚህ ሰይጣናዊ ስራው የሚገጥመዉ ምላሽም በጣም የከፋ ሊሆን ስለሚችል ለጥፋት ብቻ ትግራይ መሬት ላይ የተቀመጠዉ አቶ አባይ ወልዱ በጊዜው የያዘውን ሥልጣን እና ያስታጠቀውን ሚሊሺያ ሌላ ሊበግረው የሚችል ሃይል መሥሎት በትቢት ወይም በድንቁርና ከአንድ ጥፋት ወደ ሌላ ጥፋት መሸጋገሩ ትልቅ አደጋ ነዉ። በመላው አገሪቱ በዜግነታቸው ኮርተው፤ የሚኖሩበትን ህብረተሰብ አምነው እና ተዋደው የሚኖሩትን የትግራይ ተወላጆች በወልቃይት ጠገዴ የግፍ እሳት ላለማቃጠል ቆም ብሎ እንዲያስብ እጅግ እናሳስባለን።
ላለፉት 30 ዓመታት የቃፍቲያ ሁመራ፤ ወልቃይት ጠገዴ/ጠለምት ህዝብ የአማራ ምንነቱን ተነጥቆ፤ አማራም ጎንደሬም አይደለህም ተብሎ፤ የዘር ማጽዳት ድርጊት ተፈጽሞበታል። ለዘመናት ከኖረበት መሬት ተፈናቅሎ ብዙ ትዉልድ ለስደት ተዳርጓል። ላለመሰደድ በቀየው መሞትን የመረጠ ተወላጅ፤ እጣ ፈንታው ለዘመናት ፀሐይን እንዳያይ ተወስኖበት እስር የሚማቅቀዉን ብዛት፤ የትግራ እስር ቤቶች ይቁጥሩት። በጀምላ የተቀበረዉን ደግሞ፤ ጊዜ እያወጣዉ ነዉ፤ ክቡር ገረመድን አራያ ይናገራሉ።
የዚህን አካባቢ ህዝብ ከገደለ እና ካፈናቀለ በኋላ፤ ብዛት ያላቸውን የትግራይ ተወላጅ የወያኔ ደጋፊዎቹን ተከዜን አሻግሮ አስፍሯል። በአሁኑ ሰዓት ደግሞ ይህን ሁሉ ግፍ እና በደል ከፈጸመ በኃላ፤ በአካባቢው ለህዝበ ውሳኔ ለማቅረብ የማጥቂያ ስልት ነድፎ ተነስቷል። በቂ የወልቃይት ተወላጆች የሉምና እኔ ያሰፈርኳቸውና አንዳንድ ሆዳሞች በድምጽ ብልጫ ለኔ ድምጽ ሊሰጡ ይችላሉ ብሎ በማመን፤ የዘወትር ዉሸትና ብልጥነቱን በማጠናከር እራሱ ፌደራል ብሎ በሰየመዉ ምክር ቤት ህዝቡ ተጠይቆ ምክር ቤት ይወስናል የሚል አጀንዳ ይዞ ብቅ ለማለት እየተዘጋጀ ነዉ። ከአሁን በኋላ፤ የወልቃይት አማራም፤ ጎንደሬም የመሆን ውሳኔ የሚጸናው፤ በወልቃይት መሬት በሰፈሩ ተከዜ ተሻጋሪ የትግራይ ተወላጆች ሳይሆን፤ የመላው ጎንደር ሕዝብ ውሳኔ ነው።
ይህ የማንነት ውሳኔ ደግሞ፤ በወያኔ መሪዎች በነ አባይ ወልዱ ችሮታ የሚለገስ ሳይሆን፤ በቆራጥነት፤ እነሱ የረገጡትን ጀግንነታችን አሥመስክረን በምንጎናፀፈው ነፃነት ብቻ ነዉ።። በዚህ መልክ ቆርጠን ስንነሳ ነው፤ የጎንደር ታሪካዊ መሬት ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ ወደነበረዉ ወደጥንቱ ጎንደር ክፍለ ሃገር በአስቸኳይ ሊመለስ የሚችለው ብሎ የጎንደር ሕብረት አጥብቆ ያምናል። ይህ እንደሚመጣ ወያኔ አስቀድሞ በማወቁ፤ መላ የትግራይን ወንድ ልጅ ከመንግሥት ካዝና እየዘረፈ ሙሉ በሙሉ አስታጥቋል። ይን ለመመከት፤ ካሁን በፊት ደግመን ደጋግመን እንዳስጠነቀቅነው፤ ዛሬም እንዳለፈው፤ ለአቅመ አዳም የደረሰ ጎንደሬ በሙሉ መታጠቅ አለበት። የወልቃይት ጉዳይ፤ ከአዲስ አበባው ማስተር ፕላን በላይ በዜጎች ማንነት ላይ እዬተፈጸመ ያለ አስከፊ በደል ነው። በመሆኑም በቆራጥነት መስዋዕትነትን መክፈል፤ የማንነትም፤ የተወላጅ ባለቤትነትም፤ የዜግነት ግዴታ ነው።
ከዚያም በላይ! በጎንደር ህብረት አቋም እና እምነት ደግሞ፤ ይህ በጎንደር ህዝብ ላይ፤ ብሎም በሰፊዉ አማራ ህዝብ ላይ ያነጣጠረ የወያኔ ቱባ መሪ አባይ ወልዱ የክተት አዋጅ ወያኔ እራሱን እንደማነቅ ሲሆን፤ የኢትዮጵያን ሕዝብ አፍኖ የሚመራዉ ስርዓትም የመጨረሻዉ የሞት ጣር እና ኑዛዜ ከመሆን እንደማያልፍ እርግጠኛ ሁነን እንናገራለን። ታላቁን የአማራ እና የትግራይን ህዝብ ለማዳማት በፈጸሙት የአርባ አመታት የጭፈጨፋ እና የጥላቻ ዘመቻ በኪሳራ ስሌት እየገፋ የሁለቱ ማህበረሰብ እስከ አሁኑ ድረስ ችግርም ሆነ ደስታዉን የወያኔን ከፋፋይ መርዝ ተቋቁሞ በጋራ ህይወቱን እየገፋ ይገኛል። ይህ እንዳይደፈረስ ከታሰበ፤ “የትግራይ ህዝብ የጎንደርን መሬት በጉልበት እንድንገዛ ድጋፍ ሰቶናል” እያሉ የሥራዓቱ ሙስና እጃቸዉ የነካ ግለሰቦችን በማናገር በቴሌቢዥን መስኮት የሚያካሂዱት ቅስቀሳ በአስቸኳይ መቆም አለበት።
ሰፊዉ የኢትዮጵያ ህዝብም የአቶ አባይ ወልዱን የእርስ በእርስ ጦርነት አዋጅን በመቃወም በጎንደር ሕዝብ ላይ የተቃጣዉን ጥቃት ለመጋፈጥ አጋርነታችሁን እንድታሳዩ በአክብሮት እንጠይቃለን። እንዲሁም የብሔረ አማራ ዲሞክራሲ ንቅናቄ (ብአዴን)ብሎ የሚጠራዉ፤ የአማራን ህዝ እወክላለሁ የሚለዉ የወያኔ አጋር ድርጅት፤ የወያኔ መጠቀሚያ መሳሪያ የመሆን የባዶ ጨዋታ ዘመን አክትሞ የትግራይ ነጻ አዉጭ ግንባር የሚያካሂደዉን የመስፋፋት ዘመቻ እንቅስቃሴ ህዝቡ ተቃዉሞዉን በመግለጽ ምላሽ ለመስጠት በሚዘጋጅበት ሁኔታ ሁሉ ጣልቃ ገብቶ ተጽዕኖ ከማድረግ እንዲቆጠብ በጥብቅ እናሳስባለን።
በመጨረሻም፤ ከህዝብ አብራክ የወጣዉ ሰራዊትም የአገሩን ዳር ድንበር ከማስከበር ዉጭ የወያኔ ታዛዥ ሁኖ በዘረኛ መንግስት የተበደለ ወገኑን ተኩሶ ከመግድል እንዲቆጠብ እናሳስባለን።፤ በአሁኑ ሰዓት የኢትዮጵያ ሕዝብ ይህን አረመኒያዊ የግፍ ሥራዓት ሊሸከም ባለመቻሉ፤ በእምቢተኝነት እየተነሳሳ ያለውን ወገንህን፤ በተለይም በሽዋ፤ በወለጋ፤ በአርሲ፤ በሃረር በጋምቤላ፤ የሚያካሄደዉን ጭፍጨፋ በአስቸኳይ እንዲቆም ወገናዊ ጥሪያችን እናስተላልፋለን። እንዲሁም፤ የወያኔ መንግስትም ብዙ ደም ሳይፈስ ስልጣን ለቆ አገሪቱን የሚያድን፤ ህዝቡን የሚያረጋጋ፤ ሁሉን ያካተተ በሕዝብ የተመረጥ መንግስት በአስቸኳይ እንዲቋቋም በጥብቅ እናሳስባለን።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!

No comments:

Post a Comment