Wednesday, February 8, 2017

ሰበር መረጃ ! ! ጥር / 29 / 2009 የሰሜኑ እዝ ወታደራዊ የትጥቅ ማከማቻዎች ተፈተሹ !


በዋና እዝ ዉስጥ የሚገኙ ከፍተኛ ወታደራዊ አዛዦች በወረደላቸዉ ትእዛዝ መሰረት ወታደራዊ የትጥቅ ማከማቻዎችን እንዲፈትሹ በወጣዉ ትእዛዝ 
የ8ኛ ብረት ለበስ ክ/ጦር አዛዥ ብ/ጄ ጀማል መሐመድ፣ የ31ኛ ክፍለ ጦር አዛዥ ብ/ጄ ተስፋዬ ወ/ማርያም፣ የ35ተኛ ክ/ጦር አዛዥ ብ/ጄ ምስጋናዉ አለሙ፣ የ24ተኛ ክ/ጦር አዛዥ ብ/ጄ ሞሐመድ ተሰማ፣ የ22ተኛ ክ/ጦር አዛዥ ብ/ጄ ገ/ እግዚያብሔር በየነ የ33ተኛ ክ/ጦር አዛዥ ብ/ጄ አማሐ ገብሩ ባጠቃላይ የመሳሪያ መጋዘኖቻቸዉ ላይ ከፍተኛ ዘረፋ መፈጸሙን አምነዋል።Image result for ወታደራዊ መሳሪያዎች
በዚህም መሰረት . . . . . . ከጥቂቶቹ ዉስጥ እነርሱም በነጻነት ታጋዬች እጅ ወድቀዋል ተብለዉ የተገመቱትን የቀላል መሳሪያዎች መጠን ዘርዝረዋል...
Makarov ........Semi-automatic pistol የጎደለ (201 )
Beretta Model 38.......Sub-machine gun የጎደለ ( 191 )
UZI........Sub-machine gun የጎደለ ( 542 )
AK-103.......Assault rifle የጎደለ ( 5666 )
AK-47.......Assault rifle የጎደለ (1022 )
AKM........Assault rifle የጎደለ (993 )
PSL (rifle).........Designated marksman rifle የጎደለ ( 9_ 61 )
BM59.........Assault rifle\LMG BM-59 MK-4 የጎደለ ( 201 )
G3..........Assault rifle የጎደለ (118 )
Vz. 58........Assault rifle የጎደለ (1598)
RP-46 "Degtyaryov".........Light machine gun የጎደለ (208 )
RPD..........Light machine gun የጎደለ ('''''''')
RPK..........Light machine gun የጎደለ ( 558 ) 
DShK..........Heavy machinegun የጎደለ ( 85 )

ማስመዝገባቸዉን ተከትሎ ወታደራዊ ደህንነቱ መመሪያ አዉርዷል በዚህም መሰረት ከላይ በዝርዝር ከተጠቀሱት በተጨማሪ ያልተመዘገቡና የጠሰወሩ እንዳሉ ሁሉ የህወሃት ወታደሮች ሲኮበልሉ ያላስረከቧቸዉ የጦር መሳሪያዎች ሲታከሉበት ወታደራዊ አደጋዉ የከፋ እንደሆነ የተቀመጠ ሲሆን።
ወታደራዊ ዘረፋዉን ለመቀነስ እንዲቻል በሰሜን ጎንደር፣ በቤንሻንጉል ጉምዝ፣ በጋምቤላና፣ በምሳራቅ ኢትዮጵያ ዙሪያ በቅርበት በሚንቀሳቀሱ የሽምቅ ዉጊያ አቀንቃኝ የነጻነት ታጋዮች ላይ ደምሳሽ ወረራ ለመፈጸም ተወስኖ ወደ ተግባር ጦርነት ተገብቷል።
በዚህም መሰረት በተለየ መልኩ በሁመራ እና አካባቢዉ ላይ ትኩረት የተወሰደ ሲሆን በዚያ አካባቢ ላይ የሚደረጉ የነጻነት ሐይሎችን እንቅስቃሴ ለአካባቢ ልዩ ሐይል እና ለመከላከያ በመጠቆም የተሳተፉ ግለሰቦችን ዝርዝር የያዘ ሰነድ ለወታደራዊ ደህንነቱ ተዛዉሮለታል።
ወታደራዊ ደህንነቱ ለነዚህ የህዝብ ጠላት በተለይም የነጻነት ሐይሎችን እንቅስቃሴ ዝዉዉር ለሚጠቁሙ ግለሰቦች የሚያደርገዉን ጥበቃ ተመልክቶ በትእዛዝ መልኩ ወደታች ካወረደበት ከመስከረም / 2009 ዓ/ም አንስቶ ጠቋሚዎቹ የህዝብ ጠላቶች ማንነታቸዉ ባልታወቁ ግለሰቦች እየታደኑ እርምጃ እየተወሰደባቸዉ እንደሚገኝ ከወታደራዊ ደህንነቱ የወጣ ፍንጭ አረጋግጧል።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ !
( ጉድሽ ወያኔ )

No comments:

Post a Comment