Saturday, February 4, 2017

ሰበር ዜና በሰሜን ጎንደር ወያኔ ኋይለኛ ፍተሽ እያካሂደ ነው

    Bilderesultat for የሰሜን ጎንደር የህዝብ ተቃውሞፍተሻው የአርበኞች ግንቦት ሰባትን ትደግፋለቹ ገንዘብ ታቀብላልቹህ በሚል ማነኛውም ህዝብ ከኪሱ ከ1500 ብር በላይ ይዞ ከተገኝ ውርስና ድብድባ ይፈጸምበታል ከትክል ድንጋይ እስከ ሳንጃ - ሶሮቃ- አብራጅራ አጥቃላይ አርማጭሆ ኋይለኛ የሆነ ፍትሻ እየተካሂድ ነው በቆላ ወገራም የነጻነት ኋይሎችን ካቅማቸው በላይ በመሆኑ እነሱን ለማግኘት ወደ ዋልድባ ገዳም የወያኔ ካድሪዎች መለኩሴ መስለው በመግባት ሥለላ እያካሂዱ መሆናቸውን የውስጥ አርበኛ አርጋገጡልኝ በሊላ በኩል ፍተሻ የሚያካሂዱት ወታደሮች አብዛኛዎች ቋንቋንቸው የማይሰማ የጋምቢላና የግሙዝ ተወላጆች ኒዮር ሊሎቹም ናቸው። 

ራሳቸው እኒህ ወታደሮች እንደዚህ አሉ እኛ የተነገረን የአማራ ህዝብ ትቢተኛ ነው በዱላ በሉት እራስራሱን በሉት የተባለነው ከበላይ አካል የተላለፈ ትዛዝ ሁኖም እኛ ሥራቱን ፈልገነው ሳይሆን አማራጭ አትን እንጅ በኛ ዚጎች ላይም ስምታቹኋል በጋምቢላ ላይ በአኟክ ህዝብ ላይ እንዲት እንደጨፈጨፉት አልፎም የደቡብ ሱዳን መንግስት በባለፈው ህጻናት ሳይቀር በአሻጥር ሊጨፈጨፍ ችሏል ብለዋል ከውስጥ አዋቂ ያደርሱኝ መርውጃ ካምባጊወርጊስ ደባርቅ እንቃሽ አጠቃላይ ህዝቡን ያጋኙት በዱላና ባገኙት ይደበድቡታል አሞራው ምንአለ ባሻ ይሂን ሁሉ የምጽፍልህ እንባው እየተናነቀኝ በሆዴ እየተቃጠልኩኝ ነው የምጽፈው ከዚህ ውስጥ ግን አንድም የአማራ ወታደር ወይም የኦሮሞ ተወላጅ የሆነ መከላከያ በፍጹም አታገኝም።
 
የአማራና የኦሮሞ መከላከያ ሠራዊት በጋምቢላና በየጠረፉ ያስማሯቸው በወገናቸው ላይ የዚህ አይነት ግፍ በህዝባቸው ላይ እንደማይፈጽሙ ሰላወቀ ከጠረፍ በባድሜና በተለየዩ ቦታ የሚያስቀምጣቸው።

በሊላ በኩል የቅማንትና የአማራን ህዝብ ለማጋጨትና እርስበርስ ለማጋደል ያደረገው ሴራ ሙሉ በሙሉ በህዝቦች ንቃት ሊከሽፍ ችሏል ይሂንም ያመጣቹሁት እራሳቹህ እናተው ሁለቱ ህዝቦች የተዋለዱና በሁሉም ሥነመግባር አንድ ነን በማለት አሳፍረው መልሰውታል፡ ካድሪዎች ብቻ ናቸው ውስጥ ለውስጥ ነገሩን የሚያከባልሉት ሊሳካላቸውም አልቻሉም ያላደርጉት ነገር የለም በህዝቡ ንቁ ተሳትፎ አክሽፈውታል።
ወሎ ውስጥ በዚህ ተመሳሳይ ሞክረ ሊሳካላቸው አልቻሉም። ጎጃምም በዚህው መንገድ አሉ አሉ ህዝቡ ከነሱ ቀድሞ ነቅቶባቸዋል።
አሁን የአማራን ህዝብ በፍተሻና በማሽማቀቅ ሆን ብሎ ተያይዞታል ነገሩ ግን ለድል መብቃቱ አይቀርም።

አዳዲስ ነገር ሲኖር እመለሳለሁ።
ሞት ለገዳይ ለአምባገነኖች 
ድል ለጭቁኑ ህዝብ፡
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር በክብር ። 
ካርበኞች መነደር አሞራው ምንአለ ባሻ ነኝ#

No comments:

Post a Comment