Friday, February 24, 2017

በአንድ የክስ መዝገብ – በሽብርተኝነት ተከሰሱ !!! ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ እና ዶ/ር መረራ ጉዲና

• አንፃራዊ ነፃነት በነበረበት በምርጫ 97 በከፍተኛ የሕዝብ ድምጽ የተመረጡ የሕዝብ ተወካዮች፣
• በውስጥም በውጭም – ከሌሎች ፓለቲከኖች ሁሉ በላይ የሕዝብ ድጋፍ ያላቸው መሆኑን ያስመሰከሩ፣
• በወጣትነታቸው ጊዜ የአገራችን ጉዳይ “ያገባናል” በማለት ባመኑበት መንገድ የታገሉ፣
• በጎልማሳነታቸው ጊዜም “ትግል በቃኝ” ሳይሉ ከቀድሞው የበለጠ ዋጋ በሚያስከፍል ትግል ተሳታፊዎች፣
• ለፍትህ፣ ለነፃነት፣ ለእኩልነት፣ ለአገር አንድነት … ከፍ ያለ ዋጋ በመክፈል ላይ ያሉ፣
• በተማሪዎቻቸው የተመሰገኙ መምህራን፣
• በሙያቸው የበቁ ብዙ የአካዳሚ የምርምር ጽሁፎችን ያወጡ ባለሙያዎች፣
• ቁምነገረኖች ሆኖም ፈገግታ የማይለያቸው ዜጎች፣
• ሩቅ ዓላሚዎች፣ ቀናዎች፣ በጎ ሰዎች፣ እና
• በተመሳሳይ የእድሜ ክልል ያሉ የኢትዮጵያ ምርጥ ልጆች
እና

ኢሳት እና OMN
• የህወሓትን የሚዲያ ሞኖፓሊ የሰበሩ፣
• ጋዜጠኝነት በተዋረደበት ዘመን ሕዝባዊ ጋዜጠኛ ለመሆን እየጣሩ ያሉ፣ 
• ለታፈነ መተንፈሻ የሆኑ፣
• የነፃነት ትግላችንን የማስተባበር ትልቅ ኃላፊነት እየተወጡ ያሉ፣
• ኢትዮጵያዊያን ተቋም መገንባት የሚችሉ የመሆኑ ፍንጭ እያሳዩን ያሉ፣ እና 
• ብዙዎች እንደ ዓይኖቻቸው የሚንከባከቧቸው የሚዲያ ተቋት
በአንድ መዝገብ – በአንድ የክስ መዝገብ – በሽብርተኝነት ተከሰሱ !!!
የጋራ በደልና ግፍ አድሮ መታገል የመሰለ የሚያስተሳስር ገመድ የለም።
SOURCEዶ/ር ታደሰ ብሩ

No comments:

Post a Comment