Tuesday, September 15, 2015

የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ ሬደዮ ዜና ምንጮች የላኩልን መረጃ ያመለክታል፡፡

ህዝባዊ ወያኔ ኃርነት ትግራይ በመከላከያ በደህንነትና በፖሊስ ተቋሙ ውስጥ የሚሰሩ ከትግራይ ብሄር ተወላጆች ውጭ በሆኑ አባላቱ ላይ ጆሮ ጠቢዎችን በማሰማራት የ24 ሰዓታት ያልተቋረጠ ክትትል እያደረገ የሚገኝ ሲሆን እስሩንም ጎን ለጎን አጧጡፎታል፡፡
የህወሓት አገዛዝ በመከላከያ በደህንነትና በፖሊስ ተቋሞቹ አባላት ላይ እየወሰደው የሚገኘው የስለላና እስር ተግባር በተለይም በጎንደር ከተማና ወረዳዎች ከፍተኛ ደረጃ ላይ ደርሷል፡፡ 
በጎንደር ከተማ የ1ኛ ፖሊስ ጣቢያ መርማሪ የሆነው ማረልኝ፣ በጎንደር ከተማ 6ኛ ፖሊስ ጣቢያ አባል የሆነው አባይ አለማየሁና የጭልጋ ወረዳ ፖሊስ መርማሪ የሆነው ወርቅዬ ከሰሞኑ ከአርበኞች ግንቦት 7 ጋር ግንኙነት አላችሁ በሚል ተይዘው ወደ ወህኒ ከወረዱት የፖሊስ አባላት መካከል እጅግ በጣም ጥቂቶቹ ናቸው፡፡
http://www.patriotg7.org/wp-content/uploads/2015/09/AG7-radio-15-09-2015.mp3

No comments:

Post a Comment