Tuesday, September 29, 2015

ሑመራ ከተማ የ150 ነጋዴዎች ንብረት የሆነው የገበያ ማእከል በእሳት ቃጠሎ ሙሉ ወድሟል -

12063766_917178921707098_4961080571353682314_nቃጠለው ሓሙስ 13/ 01 / 2008 ዓ/ም ሌሊት ያጋጠመ ሲሆን የ150 ነጋዴዎች ንብረት የሆነ ከ50 ሚልዮን ብር በላይ ንብረት በቃጠለው መውደሙ ታውቋል።
ህብረተሰቡ ቃጠለው ለማጥፋት የተቻለው ቢጥርም ሊሳካ እንዳልቻለ ኑዋሪዋሪዎች ገልፀዋል።
ከሁሉም በላይ ሒመራን የምታክል ትልቅ ከተማ የእሳት ማጥፍያ መኪና መንግስት ባለማዘጋጀቱ ቅሬታቸው ኣሰምተዋል።
የቃጠለው መነሻ እስካሁን ከመንግስት የተሰጠ መግለጫ የለም።

መንግስት ለተለያዩ ምክንያት መሬቱ ሲፈልገው እሳት የማስገባት ልምድ እንዳለው ይታወቃል። ለምሳሌ በመቐለ ኢንዳስትሪ ቀበሌ በተነሳው ቃጠሎ ሱቃቸው የወደመባቸው ሰዎች መልሰው ለመገንባት ሲሞክሩ መንግስት ቦታው ለሌላ ስራ ስለፈለገው መስራት ኣትችሉም ተብለው ተከልክለዋል።
ሑመራ እነሞላ ኣስገዶም የገቡበት መንገድ ስለሆነ የጣሉት ወይም የተንጠባጠበ ቢሆንስ ማን ያውቃል።
ንብረታቸው ቃጠሎ ያወደመባቸው ዜጎቻችን ፅናት እንመኝላቸዋለን።

ህዝባችን በስንት ይቃጠል ባካቹ…?
ነፃነታችን በእጃችን ነው።
- See more at: http://www.satenaw.com/amharic/archives/10526#sthash.ggSuRYXJ.dpuf

No comments:

Post a Comment