Saturday, September 26, 2015

ርካሽ ፖለቲካን በቤተ ክርስቲያን መድረክ ላይ ===========================


ርካሽ ፖለቲካን በቤተ ክርስቲያን መድረክ ላይ
===========================
ቤተ ክርስቲያኒቱ በእዚህ ደረጃ የዘረኛ ፖለቲከኞች መቀለጃ እንደሆነች ያልገባን ይህንን ተመልክተን የህሊና ፍርዳችንን እንስጥ።
=============================
ይህ የምትመለከቱት ፖስተር አዲስ አበባ መንበረ ፀባኦት ቅድስት ስላሴ ቤተ ክርስቲያን መግቢያ በር ላይ የተለጠፈ ነው ነገ አዲስ አበባ የሚገቡት የግብፁ ፓትርያሪክ አቡነ ቴዎድሮስ እና የአቡነ ማትያስ ፎቶ ከዳር እና ከዳር ተደርጎ በመሃል የአቶ መለስ ፎቶ ተለጥፏል። ምን ማለት ነው? በሁለት ጳጳሳት ፎቶ መሀል የአቶ መለስ ፎቶ ምን ማለት ነው?
''የሰማይ ደጅ'' በተባለች ቤተ ክርስቲያን በር ላይ ይህንን መለጠፍ ምን አይነት ሃይማኖታዊ አልለውም ችግሩ ከሃይማኖቱ ስላልሆነ ግለሰባዊ ዝቅጠት ግን ነው።ይህንን የሚያህል የሀገር ገፅታ ለዓለም በሚታይበት የመስቀል ደመራ ወቅት የሚመጣ እንግዳን ከማይሆን ነገር ጋር አገናኝቶ ማሳከር አላማው ምንድነው? ርካሽ ፖለቲካን በቤተ ክርስቲያን መድረክ ላይ የምትለጥፉ እናንተ የጥጋባችሁ ጥግ መድረሻ ያጣ አልመሰላችሁም?
Getachew Bekele

No comments:

Post a Comment