Thursday, September 17, 2015

(የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ)



(የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ)
የህወሓት አገዛዝ ለሱ ታማኝ በሆኑ የመከላከያ ሰራዊቱ አባላት አማካኝነት የጠገዴን ገበሬ እየጨፈጨፈው መሆኑ ታወቀ፡፡
የአርበኞች ግንቦት 7 ታጋዮች አካባቢውን ይንቀሳቀሱበታል በሚል ጥርጣሬና ስጋት እጅግ በጣም ከፍተኛ ቁጥር ያለው የመከላከያ ሰራዊት ኃ ይል በጠገዴ ምድር ላይ ያፈሰሰው እና የጠበቀውን ድጋፍ ከህዝቡ ማግኘት ያልቻለው ህወሓት የአርበኞች "ግንቦት 7 ታጋዮችን ታስጠልላላችሁ እና መረጃ ስጡን..." በሚል ሰበብ ነው ደሃውን ገበሬ በጥይት እየጨፈጨፈው የሚገኘው፡፡
ባለፈው ሳምንት ጳጉሜ 5 2007 ዓ.ም የህወሓት መከላከያ ሰራዊት በጠገዴ ሳርና ነዋሪ ገበሬዎች ላይ በከፈተው ተኩስ አቶ አቡሃይ መኩሪያ የተባሉት ገበሬና ወንድ ልጃቸው እሸቴ አቡሃይ በአሰቃቂ ሁኔታ መገደላቸው ታውቋል፡፡

No comments:

Post a Comment