Friday, April 29, 2016

የከሸፈው የበአዴን/ህወሃት/ኢህአዴግ ስብሰባ በዳላስ!

ባሳለፍነው ሳምንት እሁድ April 24, 2016 ወያኔ/ኢህአዴግ ጠፍጥፎ የሰራው የበአዴን ከፍተኛ ባለስልጣናት ከክልሉ ተወላጆች ጋር በልማት ዙርያ እወያያለሁ በሚል የዘወትር ዲስኩራቸው ለማሰማት ወደ ዳላስ/ቴክሳስ መምጣታቸውና ስብሰባ ማድረጋቸው የሚታወስ ነው። ስብሰባው በበአዴን የዳላስ ተወካዮችና በዋሽንግተን ዲሲ የኢትዮጵያ ኢንባሲ የተዘጋጀ ነው ቢባልም ከመግቢያው በር ጀምሮ ተቆጣጣሪ የነበሩት የህወሃት/ኢህአዴግ ሰዎች ነበሩ። የክልሉ ተወላጆች ጨምሮ አያሌ ኢትዮጵያውያን ወደ ስብሰባው ስፍራ ቢያመሩም የመግቢያ ቲኬት የላችሁም በሚል ወደ አዳራሹ እንዳይገቡ ታግደዋል።
የስብሰባው አዳራሽ ባዶ እንዳይሆንባቸው የህወሃት/ኢህአዴግ አባላት የተገኙ ሲሆን በቅጡ ተቆጥረው በአጠቃላይ ከ45 አይበልጡም ነበር። ከ50,000 በላይ ኢትዮጵያውያን በሚገኙበት ዳላስ ከተማ የኢትዮጵያ ከፍተኛ ባለስልጣን መጥቶ ትንሽ ቁጥር ያለው ህዝብ ስብሰባው ላይ መሳተፉ የዳላስ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ምን ያክል በወያኔ ተስፋ የቆረጡና የተማረሩ መሆናቸውን ነው።
ስብሰባው ላይ ከተሳተፉትና ካዘጋጁት ውስጥ ተኮላ፣ ፀሃይጽድቅ፣ ኢብራሂም፣ ሙሉጎጃም ገዳሙ፣ አቶ መሰረት፣ ወ/ሮ መሰረት፣ አያሌው አርጋው፣ ወ/ሮ አለምፀሃይና ሌሎችም ይገኙበታል። ሰው በላ የሆነውን አንባገነኑና ፋሽስቱ የወያኔ/ኢህአዴግ ስርዓትን እድሜ ለማራዘም በታማኝነት ተግተው የሚሰሩት እንዚህ ጥቂት አደርባዮች ለይቶ በማወቅ አስፈላጊውን ጥንቃቄ ማድረግ ያስፈልጋል። አብዛኛዎቹ በኮሚኒቲያችን፣ በቤተክርስቲያን፣ ኢትዮጵያዊ በሆኑ የሲቪክ ማህበራት ውስጥ እራሳቸው ሸሽገው የወያኔ 52 ገፅ የዲያስፖራ ፖሊሲ ለማስፈፀም የስለላ ስራ ሲሰሩ ቆይተዋል።
እነዚህ ተላላኪ የወያኔ ተኩላዎችን ለይቶ በማወቅ እራሳችን እንጠብቅ፤ ለሌሎችም እናሳውቅ። ለሆዱ ያደረ ባንዳ ዘመድና ጓደኛው ሆዱና ሆዱ ብቻ ነውና!
የነፃነት ቀን እሩቅ አይደለም!
በፅናት እንታገል!
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!

No comments:

Post a Comment