Monday, April 18, 2016

ለጋምቤላው እልቂት ሳሞራ የኑስ እና ጄኔራል አብርሃ ማንጁስ ተጠያቂዎች መሆናቸው ተገለጸ፣ ከግድያው የተረፉ እማኞች የክልሉን የዘገየ እርምጃ አውግዘዋል ሌሎችም ዜናዎችና ሙሉ ፕሮግራሙን ያዳምጡ

የህብር ሬዲዮ ሚያዚያ 10 ቀን 2008 ፕሮግራም
<… በጋምቤላ የተከሰተው ግድያ ድንገተኛ አደጋ አይደለም በተደጋጋሚ እየተሰነዘረ የነበረ ጥቃት ነው።  ራሳቸው የሕወሓት ባለስልጣናት የሚያውቁት ነው። ጠረፍጠባቂ ማድረግ ሰራዊት እዛ መኖር ነበረበት ሀላፊነቱ የመንግስት ነውመፍትሔው ይሄን ስርዓት መለወጥ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ላይ ጫና መፍጠር ሕዝቡ በአንድላይ ለመብቱ እንዲቆም ማድረግ ካልተቻለ ግድያው ትላንትም ነበር ዛሬ አለ ነገም…> አቶ ኦባንግ ሜቶ የትብብር ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ዋና ዳይሬክተርበደቡብ ሱዳን ታጣቂዎች  የተወሰደውን ግድያ አስመልክቶ   ከሰጡን ቃለ መጠይቅ የተወሰደ     (ሙሉውን ያዳምጡት)
<…ሰራዊቱ የሕወሃት ባለስልጣናትን ንብረት፣የነሱን ስልጣን ጠባቂ አድርገውታል። ኦሮሚያ ላይ ከፍተኛ ሰራዊት አላቸው፣በመሐል አገር በተለይም ከፍተኛ ቁጥርያለው በሰሜን እዝ አለ  ባለፈው በኤርትራ ወጣቶች ተወሰዱ ሲባል ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሰራዊት አንቀሳቅሰዋል ዛሬ ግን ሰው እንኳን ሞቶፈጣን እርምጃ አልወሰዱምበዚህ ጥፋት ተጠያቂዎቹ የሰራዊቱ አመራሮች ናቸው።ሰራዊቱ ግን በአሁኑ ወቅት እየጠየቀ ነው …> ኮሎኔል ደረሰ ተክሌ የቀድሞ የሰራዊቱ የጥናትና ፕላን ክፍል ሀላፊበጋምቤላ የተከሰተውን ግድያ አስመልክቶ ለህብር ከሰጡት ማብራሪያ(ሙሉውን ያዳምጡት)
<…
በጋምቤላ የተወሰደው ግድያ ከደቡብ ሱዳን ድንበር ጥሰው የገቡት የሙርሌ ታጣቂዎች ግድያ ሲፈጽሙ የዛሬው የመጀመሪያ አይደለም። ከሳምንት በፊት ፉኢዶላይ ሃያ አኙዋኮችን ገለው ከብት ዘርፈው አፍነው የወሰዱዋቸውን ሶስት ህጻናት ገለዋል። የወያኔ ባለስልጣናት ያሉት የለም። ሕዝቡን ትጥቅ አስፈትተው እርስ በእርሱከፋፍለው እየገደሉና እያስገደሉ ያሉት እነሱ ናቸውስርዓቱ ካልወደቀ ግድያው አይቆምም።…> አቶ ኡዶል ኡጁሉ የታህሳስ ሶስት መታሰቢያ ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄዋና ጸሐፊ የደቡብ ሱዳን ታጣቂዎች በጋምቤላ በንጹሃን ላይ የፈጸሙትን ግድያ አስመልክቶ ከሰጡን ቃለ ምልልስ(ቀሪውን ያዳምጡ)
በሊቢያ በረሃዎች እና የባሕር ዳርቻዎች ላይ የዛሬ ዓመት በአረመኔዎቹ አይሲስ ታጣቂዎች በግፍ ስለተገደሉት 30 የሚጠጉ ወገኖቻችን ቅዱስ መጽሐፍ ቅዱስ ምንይላልቁርዓኑስስለ ከፈሉት ሐይማኖታዊና ኢትዮጵያዊ ተጋድሎ የሚዘክር መሰናዶ(ልዩ ጥንቅር)
በኦሮሚያ ክልል የተነሳው ሕዝባዊ ንቅናቄ በአገዛዙ የመብት ረገጣ እየተዳከመ ነውየተቃውሞ አመራሮች ተገቢውን አመራር ሰጥተዋል እና ሌሎችን ወቅታዊ ጉዳዮችአስመልክቶ ከቢቢኤኑ ዋና ዳይሬክተር ጋዜጠኛ ሳዲቅ አሕመድና ከአንሃፋው ጋዜጠኛ በፍቃዱ ሞረዳ ጋር ያደረግነው ሰፋ ያለ ውይይት የመጀመሪያ ክፍል(ያዳምጡት)
ኦቲዝም እና ልጆቻችን ወላጅና ባለሙያ ምን ይላሉ ቃለ መጠይቅ ተካቷል(ያዳምጡት)
ሌሎችም
ዜናዎቻችን
በጋምቤላ በደቡብ ሱዳን ታጣቂዎች ለተገደሉት 200 በላይ ንጹሃንና ለታፈኑት  ከመቶ በላይ ህጻናት የምዕራብ ዕዝ አዛዥ ጄኔራል አብረሃ ማንጁስና ኤታማዦርሹሙ ሳሞራ የኑሱ ተጠያቂዎች መሆናቸው ተገለጸ
ከግድያው የተረፉ እማኞች የክልሉን የዘገየ እርምጃ አውግዘዋል
አባዱላ ገመዳ ኢህአዴግ መቶ በመቶ በተቆጣጠረው ፓርላማ ተቀምጠው ጸሎት እንዲደረግላቸው መጋበዛቸው የስርዓቱ ደጋፊዎችን ጭምር አስቆጣ
የጋምቤላውን ጥቃት ተከትሎ ኢትዮጵያውያን የአገሪቱን ድንበር መጠበቅ የተሳነው አገዛዝ ላይ ቅሬታቸውን ማቅረብ ቀጥለዋል
የአረብ ኢሚሬት በአሰብ ወደብ ላይ ወታደራዊ ተቋም መገንባት ለኢትዮጵያ ስጋት መሆኑ ተነገረ
ኮስታሪካ በህገወጥ መንገድ ወደ ግዛቴ ገቡ ያለቻቸውን ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን ዳግም ወደ ፓናማ ማባረሯ በሁለቱ አገሮች መካከል ውጥረት ፈጠረ
በጣሊያኑ ላምባዱሳ ደሴት አቅራቢያ ለሰጠሙት ወገኖቻችን ተጠያቂ የሆነው ግለሰብ ጣሊያን ውስጥ ቅጣቱን አገኘ
ለስልጣኑ የሰጋው የኢትዮጵያው አገዛዝ የፈለገውን ኮምፒዩተር ለመሰለልም ሆነ የዜጎችን የዲጂታል እንቅስቃሴ ለመገደብ ሕግ አርቅቆ አቀረበ
 ሌሎችም ዜናዎች አሉ
Hiber radio Las Vegas ይህ ህብር ሬድዮ _የወቅታዊ መረጃ ምንጭ ነው። ህብር ሬድዮ በአቤኔዘር ኮሙኒኬሽን ሴንተር እየተዘጋጀ ከላስ ቬጋስ ከተማ፣ ዘወትርዕሁድ በአካባቢው ሰዓት አቆጣጠር ከምሽቱ 630 ሰዓት እስከ 8 30 ሰዓት በህብር ሬዲዮ ድህረ ገጽ ወይም በቀጥታ በስልክ ለማዳመጥ 712 -432-8451መደወል ብቻ በቂ ነው በእንግሊዝ ለምትኖሩ 01405770140 በስልክ ማዳመጥ ይቻላል። ዘወትር በድህረ ገጻችን፣  googel app store Hiber Radioወደ ስልክዎ በመጫን ካልሆነም በዘሐበሻ እንዲሁም በተጠቀሱት ስልኮች ማዳመጥ ይቻላል።

No comments:

Post a Comment