Wednesday, December 21, 2016

በኦጋዴን በተቀሰቀሰው ጦርነት የወያኔ 8 ወታደሮች መገደላቸው ተሰማ

የገዢው የህውሃት ወታደሮች በኦጋዴንም ጦርነት ተከፍቶባቸዋል። የኦጋዴን ነጻ አውጪ ዜና ኤጄንሲ እንደዘገበው በወያኔና በኦጋዴን ነጻ አውጪ ግንባር ሰራዊት መካከል ጠንከር ያለ ጦርነት ተካሂዷል።
ግንባሩ ባለፈው ሃሙስ በኦጋዴን ቃብሪዳህር ወረዳ ዲሞዲሊ መንደር ውስጥ የህወሃት ኢህአዴግ ታጣቂዎች በአካባቢው ነዋሪዎች ላይ እንደተለመደው የጅምላ ግድያ፣ አስገድዶ መድፈርና እስራት መፈጸማቸውን ተከትሎ ግንባሩ ከተጠቂዎቹ ጎን በመቆም አጸፋዊ ምላሽ መውሰዱን አስታውቋል።
በሁለቱ ቡድኖች መሃከል በተደረገው የተኩስ ልውውጥ የህወሃት ኢህአዴግ ወታደሮች ተገለው፣ 8መቁሰላቸውን የግንባሩ ወታደራዊ ክንፍ አስታውቋል። በኦጋዴን ግዛት ውስጥ የገዥው ፓርቲ ወታደሮች እና የክልሉ ልዩ ጦር በቀጠናው በተደጋጋሚ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን በከፋ ሁኔታ መፈፀም መቀጠላቸውን ግንባሩ በላከው መግለጫ አብራርቷል።

No comments:

Post a Comment