Saturday, January 14, 2017

በአልጣሽ ፓርክ የነጻነት ሃይሎችን ለማጥቃት የተላኩ ወታደሮች ከፍተኛ ጉዳት ደረሰባቸው ጥር ፭ (አምስት)ቀን ፳፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :

 ምንጮች ለኢሳት እንደገለጹት በሰሜን ጎንደር ዞን በቋራ ወረዳ አልጣሽ ብ/ፓርክ ውስጥ ለነጻነት የሚታገሉ ሃይሎችን ለመውጋት በሚል የተላኩት ወታደሮች የተወሰኑት ሲሞቱ አብዛኞቹ ደግሞ ከፈተኛ  ጉዳት ደርሶባቸዋል።Bilderesultat for የኢትዮጵያ ወታደር

በ3 ቡድን ተከፍሎ ለጥቃት ወደ ፓርኩ ከገቡት የሰራዊት አባላት መካከል   አብኑን ወይም አምዶክ ተብሎ በሚጠራዉ አካባቢ የገቡት ወታደሮች  የተጓዙት የእግር መንገድ ከመርዘሙና አብኑን ላይ አለ የተባለው ውሃ ባለመገኘቱ ለከፍተኛ የውሃ ጥም ተደርገዋል። ይህ ተከትሎ ወታደሮቹ  ውሃ ፍለጋ ሲባዝኑ እርስ በርስ አለመግባባት መፈጠራቸውን ምንጮች ይናገራሉ።

አለመግባባቱ ሰፍቶ ሶስት ወታደሮች እርስ በርስ ተታኩሰው ሲገዳደሉ፣ ከ75 በላይ የሚሆኑት ደግሞ ተስፋ ቆርጠው ተበታትነዋል። አሳሽ ሃይሉ መጥፋቱ ከተነገረ በሁዋላ በተደረገው የሄሊኮፕተር አሰሳ  57 ወታደሮች ክፉኛ ተጎድተውና ተጎሳቁለው ተገኝተዋል። እነዚሁ ወታደሮች በአሁኑ ሰአትም በባህርዳር ህክምና እየተደረገላቸው ይገኛል። የ7ቱ የመከላከያ አስከሬን ደግሞ በፍለጋ የተገኘ ሲሆን  የ11 ወታደሮች የደህንነት ሁኔታ ግን እስካሁን አልታወቀም። ከ7ቱ ሟች ወታደሮች መካከል የ6 ቱ አስከሬን የተገኘው ሱዳን ውስጥ  ዲንዲር እየተባለ በሚጠራው ብሄራዊ ፓርክ ውስጥ ነው።
ኢሳት በጅጅጋ በተደረገው የከፍተኛ ወታደራዊ አዛዦች ስብሰባ ላይ አንድ ሻምበል ጦር መጥፋቱን በተመለከተ ሪፖርት ተደርጎ እንደነበር በሳምንቱ መግቢያ ላይ መዘገቡ ይታወቃል።

No comments:

Post a Comment