Sunday, October 18, 2015

የኢህአደግ ስርኣት

በኩራዝ ወረዳ የተጀመረው የሸንኮራ አገዳ እርሻ በኗሪው ህዝብ ላይ ከፍተኛ ተቃውሞ እንደጋጠመው ታወቀ።
ከቦታው በደርስን መረጃ መሰረት ኣምባገነን ገዥ የኢህአደግ ስርኣት በክልል ደቡብ ዞን ኦሞራቴ ወረዳ ኩራዝ የሸኮራ ኣገዳ እርሻ ለመስራት በመባል የጀመረው በኗሪው ህዝብ ከፍተኛ ተቃውሞ ካጋጠመው በዉሃላ ቅደሚያ ይህን ግደብ ግልገል ግቤን መገደብ ከዚህ የፈሰሰ ውሃ እዚህ አካባቢ ለሚገኝ ህዝብ ችግር እንደሆነ በማውቅ ተቃሞ በሚያሰማበት ግዜ የገዥ ቡድን ተላላኪ የሆኑ ፈጥኖ አዳራሸ ለዚህ ኗሪ ህዝብ በመቀጥቀጥና በመጋፋት ግፍ ያደረሱ መሆኑን መረጃው አክሎ አመልከተ።
ባለ ሰልጣን ይህ ስርአት የሽኮራ አገዳ ለመሰራት ከኗሪው ህዝብ ጋር መነጋገርና መረዳዳት ሳያረግ ለመተግበር ከመሬቱ አስገድዶው በማፈናቀል ወደ በረሃ ስለጣለው ከፍተኛ ተቃውሞ ያሰሙ መሆኑ ተገለፀ።
በተመሳሳይ እስከ ኣዉህን የሚሰራ ያለ የስኮር ፋብሪካ መተሃራ፤ ወንጂ፤ ፍንጫ በተለያዩ ምክንያት ከአቅም በታች እያመረተ እንዲሆነ ቢያውቅም ሌሎች 7 አድስ ፋብሪካ ብቑ ስኮር ያምርታሉ ተብሎ ተስፋ ብደርግላቸው ተስፋ ብቻ ሁነዉ ስለ ቀሩ ለሃገር ሊሸፋን የሚችለው 6.5 ሚልዮን ኩንታል ሊያመርቱ አልቻሉም።
ሃገር ውስጥ አጋጥሞ ያለውን የስኮር አገዳ እጥረት የህዝቡን ችግር መቅረፍ ያልቻለ መሆኑን ቢታውቅም የኮርፖሬሽን ሃላፊ ለመሸፈን ቢሞክሩም ዋናው ችግሩ ግን ለሰኮር አገዳ ተብሎ የሚወጣ በጀት የሰረአቱ አመራሮች ለግል ጥቅም ስለሚያውሉት መሆኑ ተገለፀ።
ይህ በእንዲህ እያለ በአሁን ወቅት በሁሉም የሃገር ገበያዎች ኣጋጥሞዉ ያለ የስኮር እጥረት ከህንዳዊዉ “አግሮ ክሮብ ኢተረናሸናል” የተባል ድርጅት 75 ሺ ቶን ስኮር በ29.7 ሚሊዮን ዶላር ለመግዛት የተሰማማ ሆኖ መንግስት ደግሞ ጥሩ ምርት ወደ ውጪ እየሰደደ ከሌላ ሃገር ለጤና ችግር የሚያመጣ መሰብሰቡ ፀረ ህዝብ ኣስራሩ የሚያሳይ ነው ሲሉ ገለጡ።

No comments:

Post a Comment