Sunday, October 18, 2015

የኢህአደግ የመከላከያ ሰራዊት

አባላት የመንግስት የተቃዋሚ የሆኑ ሬድዮ ጣቢያ ሰምታችሁዋል እያሉ በመያዝ እያታሰሩ መሆኑ ተገለፀ።
በደረሰን መረጃ መሰረት ሁሉን የመከላከያ ሰራዊት ያሳተፈ በከፍተኛ አመራሮችን የሚመራ ትኩረት የተሰጠው ስብሰባ ወታደሩ ፈርሶ ያለማቆረጥ እግሬ አውጪኝ ብሎ ወድ አገኘበት ቦታ መጥፋቱ ፀረ መንግስት የሆኑ የተቃዋሚ የሬድዮ ስርጪት መከታተል እንደዋንኛ ምክንያት የተነሳ ሲሆን መንግስት የሚያሰራጨዉ ትተዉ የጠላት መረጃ የሚያዳምጡ መታወቅ ኣልባቸዉ በሚል ደስ ሳያሰኛቸዉ የተገኘ ወተሃደር ማሰርና ማባረር ላይ ይገኛሉ።
መረጃው ኣስከትለዉ የመከላከያ ሰራዊት አባላት ሚድያ እንዳይከታተሉ በማድረግ የስረአቱ የተለየ ተጠቃሚ የሆኑት ከፍተኛ መኮኖኖች ጥቅማቸው እንዳይጎደልባቸው ሚድያ መከታተል እንደ ወንጀል አድርገው በማቅረብ ደንብናቅ ህገ መንግሰት ከሚለው ውጪ “ደጋፊና ተቆርቓሪ የትጥቅ ትግል የሚያካሂዱ ድርጅት በዉስጣችን እንዳሉ ደርሶናል ይህን ሃሳብ የማይቀበልና የማያምን ወተሃደር ፀረ ልማታዊ መንግሰታችን የቆመ ነዉ” እያሉ ለተሰብሳቢዉ ሰራዊት እያስፈራሩ መሆኑን ተገለፀ።
እንደሚታውቀው የኢህአደግ አመራር ህዝብን አፍኖ የስልጣኑ ዕድሜ ለማራዘም በፅኑ ከሚሰራላቸዉ ኣንድ የተቃዋሚ ድርጅት ሚድያ እንዳይ ከታተል መገደብ ሲሆን። በተለይ ድግሞ ቁጥጥሩ በመከላከያ በጠነከረ መልኩ እንደሚሰራለት ባለፈው የዜና እወጃ መግለጣችን ይታወቃል፣፣


No comments:

Post a Comment