Wednesday, October 14, 2015

የቆረጠ ጀግና ድምጽ ቃለ ህይወት – ጥንካሬን ያበጃል። አንዳርጋቸው የነጻነት ፍልስፍና ነው! የቅኔ – ቃናም! -

ወያኔ በማፍያ ተግባሩ ተባባሪ በእጁ የገባለት ኢትዮጵያዊ ጀግና ከብረት ቁርጥራጭ የተሰራ መንፈስ እንደለው ፈጽሞ ያወቀ አይመስለኝም። በመጀመሪያ ነገር የተከበሩ የአቶ አንዳርጋቸው ፍልስፍናው እንዲህ በግልብ ጮርቃ አቀም ሊፈተሽ አይችልም። የጠጠረ ነው። አንዳርጋቸው ፍልስፍና ነው። ጥልቀቱ ውቅያኖስ ነው። የማለዢያ አውሮፕላን ሚስጥር ማን ፈልፍሎ አወቀው? ፍሬ ነገሩ ይህ ነው። ቅኔ ነው። ሚስጥር ነው። የተሰጣቸው ብቻ የሚተርጉሙት። የተፈቀደላቸው ሁሉ የሚቆርቡበት ድህነት ነው። ወይንም ዘመን ነው እራሱ የሚጽፈው – የገድል መጸሐፍ። ቤተሰቦቻቸው አንገታቸውን ቀና አድርገው የሚሄዱበት የትውልድ ጥሪት ነው። አቅሙ ሃጢያትን የማጽዳት ጉልበት አለው። የአቶ አንዳርጋቸው ጽናት የቀራንዮ የተራራ ስብከት ነው እኔን ሲገባኝ። ነገን አቅርቦ የሚያሳይ ፍትኃት። 1. „እኔ አሁን ከራሴ ጋር ታርቂ ሰላም አግኝቻለሁ“ የምፈልገውን መከራ በሐሴት ለማስተናገድ ዕድሉን በማግኘቴ ፍለጎቴና ቀራንዮ ተገናኝቷል ነው። የፍላጎቴ ትርጉምን ሆኜው ማዬት ችያለሁ ነው የቅኔ -ዘጉባኤው ዘረፋ ድምጸቱ። 2.„እውነቱን ነው የምልህ ለእኔ እንደ ምርቃት ነው የተቀበልኩት“
አዎን! ከአውሮፓ ህይወት ወጥቶ በዛች በአዬናት ኮሳሳ ጎጆ በርሃና በርሃና የተከላተመው፤ በበርሃ ቋያ ቆዳው የተገረፈው ለጫጉላ ጊዜ አልነበርም። ህይወትን ደስ ብሎት በሰናይ ለመገበር ነበር።  ያ ቁርጠኛ መንፈስ፣ ያ የጽንት መንፈስ ሳይዛባ – ሳይሾልክ – ሳልክደው – ሳላንዘላዝለው – ሳያንዘላልጠው ቀጥ ብሎ በሁለት እግሩ እንደቆመ  „የአናንያ፣ የአዛርያንና የሚሳል“ ስቃይ ለመቀበል በመታደሌ የሰማይ ስጦታ ምርቃት ነው። የተፈቀደልኝ ድንግሉ ረድኤቴ። የሰማዕቱን ጵጥሮስ ዕድል ባላሰብኩት መልክና ቅርጽ መፈጸሙ ሽልማቴ ነው። ክብሬ ነው። የምትፈልጉትን የበቀል እርምጃ ሁሉ አዝናንቼ ለመቀበል የተደራጀ መንፈስና አቅም አለኝ ነው። ይህ ደግሞ ለናፍቃት ሀገር ጥሪት ነው። ማንም ሰው ከቶውንም ሊደፍርው ሊያጠቁረው የማይችለው በቁሙ የጸደቀ የነባቢተ ድምጽ – የነፃነት ድወል ነው። 3.„እኔ አሁን ምንም የሚያቸኩለኝ ነገር የለም። ጥሩ እረፍት ማደረግ እፈልጋለሁ“ የአንዳርጋቸው መንፈስ አይሞትም አያንቀላፋም፣ አይደከምውም፣ አይጠወልግም፤ አይጠንዝልም እዬፈካ እያበበ ትርጉሙ እዬበለጸገ እዬተንሰራፋ ይሄዳል። ይህ የኢትዮጵያዊነት ቋሚ ራዕይ ምኞት ሞቶ የማይሞት፤ ወድቆ የማይወድቅ፤ ተደፍሮ የማይደፈር፤ ሚሊዮኖች ወታደሮች የሚሆኑለት እልፎች ዘብ የሚቆሙለት ነው። ጉዞው ግን ረጅም፤ አድካሚ፤ መሆኑን እረዳለሁ – ኑሬበትምአለሁ። ተስፋንና ድልን የሰነቀ ነገ ይኖራል። የሚፈጀውን የጊዜ እርዝምት ሆነ ትግሉ ጎሰኝነትና ኢትዮጵያዊነት መሆኑን ስለምረዳ ረቂቅ ነው። የሚያስከፍለውም ዋጋ የዚያኑ ያህል ውስብስብ ስለሆነ ድሉን ለማዬት አልጣደፍም ነው የአርበኛው መልእክት። እኔ ላልፍ ወይንም ጤናዬን ልታውኩት ትችላላችሁ ግን የምልዕቱን ፍላጎት የምትፈሩት ነገር ያ ቀደምቱ የኢትዮጵያዊነት ሰማያዊ ድንጋጌ የማይገሰገስ መሆኑ ብቻ ሳይሆን አይቀሬ መሆኑንም ላብሥርህ ነው ቅኔው። 4. „በጣም በጣም ደክሞኛል፤ በቅቶኛል እውነቱን ነው የምልህ ተረጋግቼ ያለሁበት ሁኔታ ነው“ አንድ ጊዜ ትውልድ ዬማይታካቸው ፕሮፌስር አስራት ወ/ዬስ ታስረው፤ የህዝብ ፍቅር ከህክምና ልዩ ጸጋቸው በላይ የፍቅር ዲታ ስላደረጋቸው „እንኳንም ታሰሩ“ ብዬ አዕምሮ ጋዜጣ ላይ ጽፌ ነበር። አበድሽ ወይ እስክባል ድርስ። ምንአልባት አሁንም እብደቴ አግርሽቶብኝ ይሆናል። ለአብዛኞው የነፃነት ጥማተኛ እኮ አሁን አንዳርጋቸው ጽጌ የመንፈሳችን ሀውልት ነው የሆነው። በዓለም አቀፍ ደረጃ መንፈስን በፍቅር ከመግዛት በላይ ምን የሃብት ሃብት ባለጸጋነት አለና። ለዛውም የመንፈስ። 4.1 „ተረጋግቼ ያለሁበት ሁኔታ ነው“ ይህ ሰማዕታት፤ የወንጌል አርበኞች ቅዱሳኑ ሁሉ „ሩጫዬን ጨርሻለሁ“ „ወደ አንተ ልመጣ ናፍቄያለሁ“ ያሉትን ሲያመሳጥር ነው የደሙ ልዑል ወዲ ሃሪና። ዘመን ወጣትነት፤ አፍላነት፤ ጉልምስና የተሰጠበት ቋጠሮ በተግባር እንሆ ሰከነ ነው።  ሰንበት ሆነ። እርገት ሆነ። የተከበሩ አቶ አንዳርጋቸው አደራ ተረካቢው እልፍ ስለመሆኑ ሲያጠዬቁም ነው – በልጆቻቸውም እርግጠኝነታቸውን ነው አበክረው የገለጽት። ዬትግሉን ዬተከታታይነት ተፈጥራዊ ባህሪ ነው ያዘከሩት። የ አቅማቸውን ሙሉ አቅም ቁመና ነው ያብራሩት – ፍስፍና። ይኼንኑ አብነትነቱን በአደባባይ የተከተሉ፤ የሚከተሉ እልፎች ይሆናሉ ነው – ተሳፋዊው ትንቢትም ነው። 4.2 „ደክሞኛል“ ከዚህ በላይ የሚያደክም ምን ነገር አለና? ኢትዮጵያ ለዬመን ስትንበረከክ። የመን እንኳን ደፋር የሆነ የልዑላዊነታችን ቅስም የሰበረ እርምጃ እንድትወስድ መቅኖ የሆነ ጠቀራማ የወያኔ ዘመን፤ የኢትዮጵያ አንጡራ ሃብት የፈሰሰበት የሽብርተኛው ውንበድና ደማነማ ትዕይነት ሲከውን ከማዬት በላይ ምን መንፈስን ሚያዝል ነገር አለና። ያደክማል ሴራውና ትልሙ – የሙጃው። 4.3 „በቅቶኛል“ አዎና ትውልዱ በራሱ ላይ ራሱ እዬፈረሰ ማዬቱ ስለበቃን እኔ እራሴን ሰጥቸዋለሁ። ምን ትፈልጋለህ ከእኔ? ነው አንድምታው። ሌላው ዘለግ ያለው ፍልስፍናው የበቃህ ጽናቴን ውረስ፤ መንፈሴን ታጠቅ፤ ፍላጎቴ ይምራህ፤ ቃልህን ጠብቅ፤ በጠላትህ እጅህ ብትወድቅ እንኳን እኔን ተከተል። የፈለከውን ነገር ለመፈጽም የቆረጥከብት ዓላማ የሚጋብዝህን ማናቸውም ስቃይ ሞትንም አክለህ ጠብቀው። ቀልጠህ ታበራለህ። ሙተህ እንኳን ትኖራልህ፤ ሲል መንፈሱን በደሙ አተመበት ———— ለእኔ – ለአንተ – ለአንቺ – ለእርሰዎ። 5. ምንም አይነት ጥላቻ በውስጤ የለም። ምንም አ ይነት ብስጭት የለብኝም“ 5.1 „ምንም ዓይነት ጥላቻ በውስጤ የለም“ ይህ ከሌሎች የሀገራችን የፖለቲካ የነፃነት ትግሉ መሪዎች የተከበሩት ዬአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ የተለዬው መክሊት ነው። የነጻነት ትግሉ ሚዛኑን እንዲጠብቅ አድርጎ ያቆዬው መርህ። ድልድይም። በዚህ ዙሪያ ዓለም ድንቅ ያላቸውን የተከበሩ የሰላም አባት ዬኔልሰን ማንዴላ የከወኑትን የሆደ ሰፊነት፤ የአርቆ አሳቢነት መንገድ የእኛው ከቅርባችን የነበረው ግን ያላስተዋልነው ዕንቁ የአርበኛው „ወዲ ሃሪና – የሃሪና ልጅ“ የአንዳርጋቸው የህሊናው ገጽ ነበር። የመንፈሱ ንቁ ወታደር ምህረት ነበር። የልቡ ዕወጃ ይቅርባይነት ነበር። ደሙም ቋሰኝነትን አብዝቶ የተጸዬፈ ነበር። የነርቡ ትንግርት የእናታዊነት ባህሪያነትን ያመነጨ ነበር። መርኽና መንገዱም ይቅርታ ነበር። ይህን ጸጋ በመሆን አቶ አንዳርጋቸው አሳይተውናል። እንዲያውም የሚታሙበትና የሚወቀሱበት መሰረታዊ ጉዳይ ነበር። መሆን መቻል በተሰጣቸው ብቻ ይተረጎማል።  መሆን በዳር፤ በጠርዝ፤ ጫፍ ላይ ሳይሆን በፍሬ ነገር አስኳል ላይ ያርፋል –  ያፈራልም። ፍጥረትም – የወንድ ዘርና የእንቁላል ሴል እንዲሁ ነባቢተ ነፍስን በተባረከላቸው ቦታ ተዋህደው ይፈጥራሉ። የአቶ አንዳርጋቸው ህልምና ራዕዩ በቋሳ የበከተ በትን መንገድን መከተል ፈጽሞ አልነበረም። ቁስልን እዬቀረፈፉ መግልን ማዝነብ አልነበረም። ይልቁንም መካራውን ሁሉ በሆደ ሰፊ አሰተናግደን፤ የቀደምትን የእናት ሀገራችን የአብሮነት መንፈስ በክብር ወደ ዙፋኑ መመለስ ነበር። ሩጫው ይኼው ነበር። ይህ መንገድ የሚስከፋን ልንኖር እንችል ይሆናል። ስለምን? ከጎሳ ፖሊሲ መንጭቶ፣ ከዘርኝት ማህጸን ተፈልፍሎ በነፍስ ወከፍ ከዜግነት ጽንሰ – ሃሳብ ጀምሮ በዚህ ዙሪያ የተፈጠሩ አምክንዮዎችን በጠላትነት ከትክቶ ማገዶ ያደረገው የዘረኛው የወያኔ ማፍያ ቡድንና ጦሱ ዘመን ይቅር ሊለው የማይገባ ስለሆነ ነበር። በዚህ ዙሪያ የደማችን – የአካላችን – የትግራይ ጉዳይ ወይንም ትግራይን የሚገልጹ ነገሮች ሁሉ የሚያንገሸግሻቸው – የሚኮሰኩሳቸው – የሚያንገፈግፋቸው ወገኖችን ሁሉ እልፍ ናቸው። ይህ መንፈስ ነገን ሊያቆይ እንደማይችል በአቶ አንዳርጋቸው ሥር የሰደደ አመኔታና ትጋት እንዲሁም ታማኝነት ለኢትዮጵያዊነት አበልጽግ ነበር። በደልን ችሎ፤ አብሮነትን ሰንቆ፤ ትውልድን ለሀገር አደራ ማዘጋጀት፤ ማሰናዳት በአዝማችነት የግንባር ሥጋ መሆን ታላቁ የተሰጣቸው ሰማያዊ ብቸኛ ተልዕኮቸው ነበር። ይህን አስፈሪ መስመር በድፍረት – በግንባር ቀደምትንት ለመገረዝ ነበር ሳህል፤ አፋቤት በርሃ ሲንከራተቱ የነበረው። መድረክ ላይም ሁለት ጊዜ አግኝቻቸው ያሰተማሩኝ ይህን ነበር። ለዚህም ነው የጎሳ በሽተኛው በለመደው መልክ ቃሉን ቋራርጦ እንደሚያቀርበው እያወቁ ፤ መስሎ ደም ጠብቶ ከምልዕቱ ህዝብ የተሰረዘው የሚያውቁትን የብዕር ልጥፍ ትል ግለሰብ ሳይቀር ፍቅር የቀለበ ብቃቱ መካራን ገራ። ለእይሁድ የገዳይነት ፈቃድ ፈጻሚ ሆነ ተባባሪ ፈገግታ በድንግልና ሸለመው። እውነት ፈተናን የረታ አቅሙ አጥንትን ያለመልማል። የቆሰለን እልህ ይፈውሳል። መካራ ላይ ተሁኖ አይዛችሁን ያውጃል። በርቱን ላከ። መጽናናትን አናገረ። 6. „ምንም ዓይነት ብስጭት የለብኝም“ ዓላማዬን ለማስፈጸም ስንቀሳቀስ የሚደርስውን ሁሉ ማናቸውንም መስዋእትንት ለመቀበል ሃላፊነቱን የመውሰድ አቅሙም ችሎታዬም እንደ ወትሮው ዛሬም አለ – ንብረቴ ነው። ህይወቴ መከራ ነው። ስልጥኜ – ተመርቄበታለሁ። ሰልጥኜ የተመረቁበትን መከራን የመቀበል – የመፍቀድ – የመውድድ ተመክሮዬ ሁሉንም አዝናንቶ ለመቀበል ዝግጁ ነው። ስንዱነቴ ዛሬ ሳይሆን ስጀምረው ትግሉን ነበር። አሁንም ያ የሚፈለቅ መንፈስ አልሸፈተም፤ አልሻገተም ሽሁራር አልጎበኘውም በውስጤ ይንቀለቀላል ከታዬህ! ቅቤ ያጠጣል። ትውልድን ያሰናዳል። 7. „ምንም ዓይነት መጥፎ ስሜት አይሰማኝም። የመጨረሻ እርጋታና እረፍት ውስጥ ነው የለሁት“ ጀግንነትን ለሰነቀ የተግባር ጌታ ሐሤቱ ነው በቃሉ መገኘት። ወዶ ነው ማናቸውንም ጥቃት የሚቀበለው። ጸጋ ለተሰጣቸው እንዲህ ይገለጻል። እንዲህ ያምርበታልም። አምላካችንም ቀራንዮ ላይ ይህን አስተገባ። 7.1. „እርጋታ“ የድርጅት ሰው የመጀመሪያ ረድፍ መለኪያው ቁጭ ብሎ ፍላጎቱን ማዳመጥ መቻል ነው። አንድ ድርጅት ሌሎችንም ሁኔታ በተረጋጋ ሁኔታ የማስተናግድ አቅም ሊኖረው የሚችለው በመርጋጋት ተፈጥሮው ብቻ ነው።  ለዚህ ደግሞ ተፈጥሮዬ እኔን የሚገልጸኝ ይሆናል ነው። ስሜታዊነት – ረብሻ – ህውከት – ያለሰከኑ የበቀል እርምጃዎች ተፈጥሯዊ መረጋጋቴን ያፋፉታል። እኔው እራሴ የድርጅት ተፈጥሯዊ ባህሪ አለኛና። ለዚህም ነው ለመበቀል የፈለጋችሁኝ። ለማደን የደከማችሁት። ገላጻው የእቅም ምጠኔ ልኬታ ይሰብካል። ይመትራልም። እርግጥ ነው ከማህበራዊ ንቃተ ህሊና መንፈሳዊ ሃብታት ውጪ ያሉ የአካሎቻችን ክፍሎች የሰው ልጅ ብረት አይደለም። እንደ ሰው ዱላው፤ ጥቅጠቃው፤ ስቃዩ፤ ሊያስከትለው የሚችል ህመም፤ መጎሳቆሉ፤ መታመሙ፤ አካል መጉደሉ ባለፈም ሞት አይቀሬ መሆኑን። ይህ ግን የመንፈስ ጽናትን የሚለውጥ ወይንም የሚሸቅጥ አለመሆኑን በፈለገው መልክ ጎሽቶ የቀረበው የምስል ቅንበሩ ለእኔ የተራራው ስብከት ነው የሆነልኝ። ወደ 60 ጊዜ አይቸዋለሁ። አደማጭዋለሁ። እንዲጠራኝ ስለፈቀድኩለት። ግሩሙ ነገር የ ቀጣፊው ኢቲቪ አቅራቢ ምንና ምንን  ለማግናኘት ታስቦ „ተመስገን በዬነ“ እንዲያቀርበው እንደተፈለገ እናውቀዋለን። ይገባናል። ለምን ያን ጎቶቸው አልሆነም ዛሬ?! ዬጦርነቱ ብልቱ ከገባን። እንዲህ ያለ ረቂቅ ደባና ውንብድና ነው ሀገር ተጋድማ እዬተረደች ያለችው። በራስህ ራስህን ስትገድል ለሆድ ተገዝትህ። ለእኔ ለሥርጉተ ኃይልና ብርታት ሰጥቶኛል፤ ስለ ትናንቱ ነፃነት ቁጭ ብዬ እራሴን እንድፈትሽበት፤ ኢትዮጵያዊነትን በሚበክሉ ጉድፍቶች ሳይበከሉ ጽዱዑ መሆን በራስ የመተማማን መንፈስን እንደ ዕንቁ እንደሚያበራው አንብቤበታለሁ። ከዚህ ያፈነገጠ ማናቸውንም የባንዳ ቅርጥምጣሚ ንክኪዎችን ሁሉ ደግሞ መጸዬፍ እንዳለብኝ ተመክሮን ዝቄበታለሁ። እኔ እራሴ ቀጥ ያለ ፈጽሞ የማያወላዳ አቋምም ቢኖረኝም ግን አምሮ ታደሰ። እንደ እራስ ለመኖር መፍቀድ ከክብር በላይ ክብር ስለመሆኑ እንድፈትሽው ጠርቶኛል ከምል ከደሜ ጋር ተቀላቀለ ብለው ይሻላል። እንዲያውም ጫካ ስገባ ከገጡሙኝ ፈተናዎች፤ እኔ እስር ቤት እያለሁ ከገጠመኝ የመንፈስ ቅጥቀጣ ካጠነከረኝ በላይ ዛሬ ጉልበታም ጥግ መንፈሴ አግኝቷል ብዬ በእርግጠኝነት ልናገረው። እውነት ለመናገር እራስን ሳያውቁ መኖር ጸጸት ይተክላል። ሙሴያችን በሚገባ ውስጡን አላዬነውም ነበር ልበል ይሆን? ይፈቀዳል? ዛሬ ግን ቤታችን አይደለም የደማችን አዲስ ጥበባዊ ቋንቋችን ሆኗል። ይህ ከተጋድሎ የተቀዳ የመስዋዕትነት ቀንዲልነት ነው።  ለአዲስ ምዕራፍ አዲስ ንድፍዊ ስኬት አቅምን መገንባት ያስችለን። አትኩሮታዊ ፍቅር ካልፈገነው። ወቅቱን ማድመት ከቻልን። ይርዳን  አምካችን። አሜን! አብረን በመቆዬታችን ሃሳብ ማረፊያ አገኘ። ፍቅር ሲታከልበት ሃሳብ የራስ ይሆናል። የራስ ሲሆን ንብረትነቱ የሁሉም ይሆናል። እግዚአብሄር ይስጥልኝ።   ሊንክ http://ecadforum.com/ethiopianvideo/2014/07/09/ethiopian-television-etv-shows-andargachew-tsige/ ቅንብርና ድምጽ የተከደነው ሲሳይ ባለቤት የእንደልቡ ወርቁ። ኢሳቶች እባካችሁን ይህ ከወርቅ ፍልቀት የነጠረውን የድምጽ ልዩ ምት የዘወትር የራዲዮ ሆነ የቴሌቪዥን መግቢያችሁ አድርጉት። አቡነ ዘሰማያታችን ይሁን። መልዕከት የኋንሳችን ይሁን የሳላት መግቢያችንም ይሁን። „ለአንቺ ነው ኢትዮጵያንም“ ባሊህ በሉት ከትህትና ጋር። ለእኔም በራዲዮዬ የመጀመሪያ ረድፈኛ አዝማቾች ይሆናሉ። (Radio Tsegaye ወይንም www.tsegaye.ethio.info Aktuell Sendung www.lora.ch.tsegaye) ቀጣዩ ፕሮግራሜ ናፍቆኛል። ሌላው ሊንክ http://www.zehabesha.com/amharic/archives/32219 ሙሉውን ቃል ካለግድፈት እንድጽፈው ያደረገኝ ነው። - See more at: http://www.zehabesha.com/amharic/archives/32347#sthash.oHTz9vO3.dpuf

No comments:

Post a Comment