Sunday, October 11, 2015

መልእክት ለወጣቶች፤ (በወጣቶች ጉዳይ መምርያ)

patriots-ginbot-7-youth-pr
ወጣት ለአገር እድገትና ብልጽግና የሚያበረክተው አስትዋጾ ከፍተኛና በቀላሉ ለውጥ ማምጣት የሚችል ኃይል ያለው የህብረተሰብ ክፍል መሆኑ ይታወቃል። ይህን በቀላሉ ለውጥ ማምጣት የሚችል ትውልድ ጊዜው በሚጠይቀውና ለአገራችን በሚበጅ መልኩ ማደራጀት፣ መምራትና ንቅናቄው ለሚያደርገው የነጻነት፣ የፍትህና ዲሞክራሲ ትግል ግንባር ቀደም ሁኖ እንዲሰለፍ ማስቻል የንቅናቄያችን አርበኞች ግንቦት ሰባት ዋና ተግባር ነው። ስለሆነም ንቅናቄያችን ወጣቱ ትውልድ ለአገር እድገትና ዲሞክራሲያዊ ግንባታ የያበረክተው አስትዋጾ ከፍተኛና አስፈላጊ መሆኑን ግንዛቤ ውስጥ በማስገባት የወጣቶች ጉዳይ መምሪያን አቋቁሞ ወጣቱን የህብረተሰብ ክፍል ትግሉን እንዲቀላቀል በማድረግ ላይ ይገኛል።

መምርያው የተቋቋመበት ዋና ዓላማ ወጣቱ ትውልድ የወያኔን ፈላጭ ቆራጭ አገዛዝ፣ ኢ_ዲሞክራሲ፣ ኢ_ሰባዊ ድርጊት እና የሚያራምደውን የዘር ፖለቲካ በአጠቃላይ የወያኔን አምባገነናዊ ስርዓት በሚገባ እንዲገነዘብ በማድረግ እንዲሁም የንቅናቄያችንን ዓላማና ግብ በማስረዳት ለነጻነት፣ ፍትህና ዲሞክራሲ ለሚደረገው የሁለገብ ትግል ወጣቱ ትውልድ ድርሻውን እንዲወጣ ማድረግ እና ኢትዮጵያ አገራችንን ጠብቆና አስከብሮ ለትውልድ የማስተላለፉን ኃላፊነት እንዲረከብ ማስቻል ነው።

እንደሚታወቀው የአንድ አገር ቀጣይነት ያለው እድገት የሚለካው በአላት መሠረተ ልማት፣ ቁሳዊ ሃብትና ንብረት ብቻ ሳይሆን በዋናነት ይህን ተረክቦ በአደራ ለትውልድ ማስተላለፍ የሚችል ትውልዳዊ ትስስር ሲኖር ነው። ይህንንም የአገርና የህዝብ አደራ ድልድይ ሆኖ ከትውልድ ወደ ቀጣዩ ትውልድ የሚያስተላልፍ ወጣቱ የህብረተሰብ ክፍል ስለሆነ ኢትዮጵያን ከወያኔ የጨለማ ቡድን መታደግ ለነገ የማይባይል አገራዊ ግዴታ መሆኑን ተገንዝቦ ወጣቱ ትውልድ ኃይሉንና አቅሙን ተጠቅሞ የእራሱን ነጻነት በእራሱ ማወጅ እንደሚችል መምርያው ያሳስባል።
በማንኛውም አገር፣ ጊዜና ዘመን እያንዳንዱ ትውልድ የአገሩ ወራሽ፣ ተተኪና ተረካቢ፣ ጠባቂና ለሚቀጥለውም ትውልድ የማውረስ፣ የማስተላልፍና የማስረከብ ኃላፊነትና ግደታ አለበት። ስለሆነም አገርን ከእነ ሙሉ ክብራ ለሚቀጥለው ትውልድ ማስተላለፍ የእኛ የወጣቶች የዜግነት ግዴታ መሆኑን ተረድተን ጥልቅ በሆነ አገራዊ ስሜት በሦስቱም ዘርፍ ማለትም በማህበራዊ፣ በምጣኔ ሃብታዊና በፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ ከፍተኛ አገራዊ ተጽዕኖ ማድረግ እንደሚቻል በእርግጠኝነት የወጣቶች ጉዳይ መምርያ በድጋሚ በአጽንኦት ያሳስባል።
ውድ የአገራችን ወጣቶች ሆይ፤
የምንወዳትና የምንሳሳላት ብርቅዬ የጀግኖች አገር ኢትዮጵያ በባንዳዎች ወያኔ ለ24 ዓመታት የጥፋት ዘመቻ እየተካሄደና እየተፈጸመባት ሉዓላዊነቷ ተንቆ ትገኛለች። አምባገነኑ የወያኔ ቡድን በጠበንጃ ኃይል ስልጣን ከያዘበት ጀምሮ ሰብአዊ መብታችን ተጥሶ፣ ዲሞክራሲያዊ መብት ተነፍጎን፣ ተፈጥሮአዊ መብታችን ተነጥቆ፣ የዜግነት ማንነታችን ባንዲራችን ሳይቀር ተቀይሮ፣ ብሔራዊ ሃብትና ንብረት እየተዘረፈ፣ የአገራችን አርሶ አደር ለም መሬቱ እየተሸጠ፣ እተነጠቀና እየተባረረ፣ ለአገር የሚታገለው ንጹህ ዜጋ ፀረ ሰላም ፀረ ህግ ፀረ መንግሥት በመባል የሽብርተኛ ሕግ ወጥቶለት እየታሰረ፣እየተገደለና እየሞተ፣ እየተፈናቀለና እየተሰደደ፣ በግፍና በጭቆና ላይ መሆኑን ለአንተ ንቁ ህልሊና ላለህ ወጣት ትውልድ የተሰወረ አይደለምና በጽኑ በአስቸኳይ ታገለው። ነጻነትን አውጅ፤ ፍትህን ተቀዳጅ!ታሪክህን መልስ! ወያኔን ይብቃህ ከህዝብ ላይ ውረድ በለው።
ውድ የአገራችን ወጣቶች ሆይ፤
አገራችን ኢትዮጵያ ለብዙ ሺህ ዘመናት በነፃነት በቀደሙ አባቶቻችን ተጠብቃ የቆየችው በአካልና በደም ዋጋ ነው። በዚህም የኢትዮጵያ ሕዝብ ቆራጥነትና ፅናት አገርን በነፃነት መጠበቅ በዓለም ፊት ትልቅ ምሳሌነትን ያተረፈ፣ ዛሬ ለአለነውና ለመጭውም ትውልድ የሚኰራበት ሕያው የታሪክ አለኝታ፣ መመኪና ክብር ያለን ውድ ህዝቦች ነን። ይህ አኩሪ ታሪክ ፣ የዘላለም ሃብታችን በመሆኑ ጠብቀንና አስከብረን ለትውልድ ለማስረከብ ኃላፊነቱ በዋናነት የእኛ ወጣቱ ነው። ይህን እውነታ ተቀብሎ አገርን በነፃነት ለመጠበቅ ደፋ ቀና ከሚሉ ኢትዮጵያውያን ጋር አገራዊ ኃላፊነትንና ግዴታን ለመወጣት ዝግጁና ብቁ ሆኖ መታገል በእጅጉ ያስፈልጋል። ስለዚህ የአገራችን ወጣት ሁላችሁ ሰላም፣ ነጻነት፣ ፍትህና ዲሞክራሲ የሰፈነባት ኢትዮጵያን ለመገንባትና አገራዊ ድርሻንም ለመወጣት በህብረት ተነስ!፣ ታጠቅ!፣ ሰው ሁን! ታሪክህን መልስ!አረመኔው ወያኔን በቃህ በለው!
በአጠቃላይ እኛ ወጣቶች ለአገር ነጻነት፣ ፍትህና ዲሞክራሲ ለሚደረገው ትግል የወጣትነትን አቅምና ኃይል ተጠቅመን የታሪክ ባለቤት እንሆን ዘንድ በሁለገብ ትግል የኢትዮጵያን ጠላት ወያኔን ለማስወገድ ከሚታገለው አርበኞች ግንቦት ሰባት ለአንድነትና ለዲሞክራሲ ንቅናቄ ጋር በመቆም ሰላም፣ ነጻነት፣ ፍትህና ዲሞክራሲ የሰፈነባት ኢትዮጵያን ለመገንባት እና በጽናት አረመኔው ወያኔን ከህዝባችን ጫንቃ ላይ ለማስወገድ የበኩላችንን ኃላፊነትና ግዴታ መወጣት አለብን።
እንዲሁም አገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን አገራችን የጣለችብንንና የሚጠበቅብንን አገራዊ ኃላፊነት በትጋትና በንቃት መወጣት የሁላችንም ግዴታ መሆኑን ተገንዝበን ለአገር እድገት የጀርባ አጥንት የሆነውን የህብረተሰብ ክፍል ወጣቱን ከወያኔ ትውልድ ገዳይና አገር ሻጭ አገዛዝ መታደግ ተቀዳሚ ተግባር በማድረግ ትግላችንን ይበልጥ ማጠናከር እንዳለብን በጥብቅ ለማሳሰብ እንወዳለን።
ወጣቱ ትውልድ ጊዜውን፣ ኃይሉን፣አቅሙንና ጉልበቱን ተጠቅሞ ለአገርና ለእራሱ ነጻነት እንዲታገል ምቹ ሁኔታወችን መፍጠር፣ ወኔና አገራዊ ስሜት እንዲኖረው መቀስቀስ፣ ወጣቱ ትውልድ በንቃትና በቁርጠኝነት ትግሉን በባለቤትነት ተረክቦ የድልና የነጻነት ዓርማ እንዲያውለበልብ ማድረግና ጥቅሙንም ማስገንዘብ የሁሉም የህብረተሰብ ክፍል አገራዊ ተግባርና ኃላፊነት መሆኑን ተገንዝበን ሁላችንም ወጣቱን ትውልድ ከወያኔ ለመታደግ የድርሻችንን መወጣት ይኖርብናል።
በመጨረሻም ዘመኑ በአፈራቸው የብዙኃን መገናኛ መንገዶች በመጠቀም ለወጣቶች ወጣት ተኮር መልክቶችን በቀጣይነት ማስተላለፈ ስለተፈለገ በማነኛውም መንገድ ወጣቱን ለትግል ሊያነቃቃና አገራዊ እውቀት ሊያስጨብጥ የሚችል ግብዓት በመስጠት ትውልድ የማዳንና የማፍራት ተልእኮን እንድትጋሩ የወጣቶች ጉዳይ መምሪያ መልእክቱን በአክብሮት ያስተላልፋል።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!
የአርበኞች ግንቦት 7 ወጣቶች ጉዳይ መምር

No comments:

Post a Comment